Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለዕ​ዝራ ጥያቄ የተ​ሰጠ መልስ

1 መል​አ​ኩም መለ​ሰ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ልዑል ይህን ዓለም፥ አዳ​ም​ንና ከእ​ርሱ የተ​ወ​ለ​ዱ​ት​ንም ሁሉ በፈ​ጠ​ራ​ቸው ጊዜ ቍርጥ ፍር​ድ​ንና ቅጣ​ቱን አስ​ቀ​ድሞ አዘ​ጋጀ።

2 አሁ​ንም ከቃ​ልህ የተ​ነሣ አስ​ተ​ውል፤ እን​ዲህ ብለ​ሃ​ልና፦ ‘ክፉ ልብ ከእኛ ጋር ያድ​ጋል፤

3 በም​ድር የሚ​ኖ​ሩም ስለ እርሱ ይፈ​ረ​ድ​ባ​ቸ​ዋል፥ አእ​ምሮ ሳላ​ቸው ይበ​ድ​ላ​ሉና፥ ሕጉ​ንም በል​ቡ​ና​ቸው ተቀ​ብ​ለው ትእ​ዛ​ዙን አል​ጠ​በ​ቁ​ምና፥ ሕጉ​ንም ተም​ረው የተ​ቀ​በ​ሉ​ትን ሕጉ​ንና ትእ​ዛ​ዙን ትተ​ዋ​ልና።

4 እን​ግ​ዲህ በቍ​ርጥ ፍርድ ቀን ምን ይሉ ዘንድ አላ​ቸው? በኋ​ለ​ኛው ዘመ​ንስ ምን ይና​ገ​ራሉ?

5 ልዑል በዚህ ዓለም የሚ​ኖሩ ሰዎ​ችን ምን ያህል ታገ​ሣ​ቸው? ነገር ግን ስለ ወሰ​ነው ጊዜ ነው እንጂ ስለ እነ​ርሱ አይ​ደ​ለም።”


ከፍ​ርድ በፊት ያለ የሙ​ታን ሁኔታ

6 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “በፊ​ትህ ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን ካገ​ኘሁ ይህ​ንም ለባ​ሪ​ያህ ንገ​ረው፤ በሞ​ትን ጊዜ፥ ከእኛ ከእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ች​ንም ነፍ​ሳ​ችን በም​ት​ወ​ጣ​በት ጊዜ ቍርጥ ፍር​ዱን የሚ​ያ​ደ​ር​ግ​በት ጊዜው እስ​ኪ​ደ​ርስ ድረስ ይጠ​ብ​ቁ​ናል? ወይስ ከዛሬ ጀምሮ ይፈ​ረ​ድ​ብ​ናል?”

7 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ይህ​ንም እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ አንተ ግን ከከ​ሓ​ድ​ያን ጋር አት​ጨ​መ​ርም፤ ከሚ​ፈ​ረ​ድ​ባ​ቸ​ውም ጋር አት​ቈ​ጠ​ርም።

8 በል​ዑል ዘንድ የተ​ዘ​ጋጀ መዝ​ገብ ለአ​ንተ አለ​ህና፥ ነገር ግን እስከ ኋለ​ኛው ቀን ድረስ አል​ገ​ል​ጥ​ል​ህም።

9 የሞ​ትስ ነገር እን​ዲህ ነው፤ ከል​ዑል ዘንድ የት​እ​ዛዝ ቃል ከመጣ በኋላ፥ እገሌ ይሙት ባለ ጊዜ ነፍሱ ከሥ​ጋው ትለ​ያ​ለች፤ ዳግ​መ​ኛም ወደ ሰጣት ትመ​ለ​ሳ​ለች፤ ለል​ዑል ጌት​ነ​ትም አስ​ቀ​ድማ ትሰ​ግ​ዳ​ለች።

10 የል​ዑ​ልን መን​ገ​ዶች ካል​ጠ​በቁ፥ የል​ዑ​ልን ሕግ ካቃ​ለሉ፥ እር​ሱ​ንም መፍ​ራ​ትን ካላ​ሰቡ ከከ​ሓ​ድ​ያን ወገን ከሆኑ ግን፥

11 እነ​ዚያ የኃ​ጥ​ኣን ነፍ​ሳት ይዞ​ራሉ እንጂ ወደ ጻድ​ቃን ማደ​ሪያ አይ​ገ​ቡም፤ ከዚህ በኋላ መከራ ይቀ​በ​ላሉ፤ ይጨ​ነ​ቃሉ፤ ያዝ​ና​ሉም፤ ሰባ​ቱ​ንም ሥር​ዐ​ታት ያሳ​ዩ​አ​ቸ​ዋል።

12 መጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ሥር​ዐት ይህች ናት፤ የል​ዑ​ልን ሕግ ክደ​ዋ​ልና።

13 ሁለ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ ዳግ​መኛ በሕ​ይ​ወት ይኖሩ ዘንድ መመ​ለስ አይ​ቻ​ላ​ቸ​ው​ምና።

14 ሦስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፥ በል​ዑል ሥር​ዐት ላመኑ የተ​ዘ​ጋ​ጀ​ላ​ቸ​ውን ዋጋ ያያ​ሉና።

15 አራ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ በኋላ ዘመን የሚ​ጠ​ብ​ቃ​ቸ​ውን ፍርድ ያያ​ሉና።

16 አም​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ መላ​እ​ክት የጻ​ድ​ቃ​ንን ነፍስ በማ​ደ​ሪ​ያ​ቸው ውስጥ በብዙ ዕረ​ፍት ሲጠ​ብ​ቋ​ቸው ያያ​ሉና።

17 “ስድ​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ ከዛሬ ጀምሮ የሚ​ያ​ገ​ኛ​ቸ​ውን መከራ እያ​ዞሩ ያሳ​ዩ​አ​ቸ​ዋ​ልና።

18 ከነ​ገ​ር​ሁህ ሥር​ዐ​ታት ሁሉ የም​ት​በ​ልጥ ሰባ​ተ​ኛ​ዪቱ ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ በፊቱ ይፈ​ረ​ድ​ባ​ቸው ዘንድ ያላ​ቸው ዛሬ በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸው ሳሉ እር​ሱን የበ​ደሉ በፊ​ታ​ቸው የል​ዑ​ልን ጌት​ነት ባዩ ጊዜ በኀ​ሣር ይቀ​ል​ጣ​ሉና፥ በኀ​ፍ​ረ​ትም ይጐ​ሳ​ቈ​ላ​ሉና፥ በፍ​ር​ሀ​ትም ይጠ​ወ​ል​ጋ​ሉና።

19 “የል​ዑ​ልን ሕግ የጠ​በቁ ግን ከመ​ዋቲ ሥጋ​ቸው በሚ​ለ​ዩ​በት ጊዜ ሥር​ዐ​ታ​ቸው እን​ዲህ ናት።

20 በኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ያስ​ተ​ማ​ራ​ቸው የል​ዑ​ልን ሕግ ይፈ​ጽሙ ዘንድ መከ​ራ​ቸ​ውን ታግ​ሠው ሁል​ጊዜ በድ​ካም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተገ​ዝ​ተ​ው​ለ​ታ​ልና።

21 ስለ​ዚህ ነገ​ራ​ቸው እን​ዲህ ነው።

22 መጀ​መ​ሪያ የተ​ቀ​ባ​ያ​ቸ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ጌት​ነት በብዙ ደስታ ያያሉ፤ ወደ ሰባ​ቱም ሥር​ዐ​ታት ይወ​ስ​ዷ​ቸ​ዋል።

23 መጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ በዛ​ሬው ሕይ​ወ​ታ​ቸው በሞት እን​ዳ​ያ​ስ​ታ​ቸው በእ​ነ​ርሱ ያለ ክፉ አሳ​ብን ድል ይነሡ ዘንድ በብዙ ድካም ተጋ​ድ​ለ​ዋ​ልና።

24 ሁለ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ የኃ​ጥ​ኣ​ንን ነፍ​ሳት በሚ​ዞ​ሩ​በት ያዩ​አ​ቸ​ዋ​ልና፤ የሚ​ጠ​ብ​ቃ​ቸ​ው​ንም ፍርድ ያያ​ሉና።

25 ሦስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፥ በሕ​ይ​ወት ሳሉ በሃ​ይ​ማ​ኖት የተ​ቀ​በ​ሉ​ትን ሕጉን እንደ ጠበቁ የፈ​ጠ​ራ​ቸው ምስ​ክር ይሆ​ን​ላ​ቸ​ዋ​ልና።

26 አራ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፥ መላ​እ​ክት እየ​ጠ​በ​ቋ​ቸው ብዙ ደስታ ባለ​ባ​ቸው ማደ​ሪ​ያ​ዎ​ቻ​ቸው ከዛሬ ጀምሮ የሚ​ያ​ር​ፉ​ትን ዕረ​ፍ​ትና የሚ​ቈ​ያ​ቸ​ውን ክብር ያያ​ሉና።

27 አም​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ ዛሬ ያለ​ውን ሞት እን​ዴት ድል እን​ደ​ነ​ሡ​ትና ኋላ ያገ​ኙት ዘንድ ያላ​ቸ​ውን እንደ ወረሱ አይ​ተው ደስ ይላ​ቸ​ዋ​ልና፤ ዳግ​መ​ኛም ድካ​ምን ከተ​መላ ከዚህ ከጠ​ባቡ የተ​ነሣ እን​ደ​ታ​ገሡ፥ ያን ሰፊ​ውን ሕይ​ወት እን​ደ​ሚ​ያ​ገኙ ያያሉ። ሞት በሌ​ለ​በ​ትም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

28 ስድ​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ ፊታ​ቸው እንደ ፀሐይ እን​ደ​ሚ​ያ​በራ፥ ብር​ሃ​ና​ቸ​ውም እንደ ከዋ​ክ​ብት እን​ደ​ሚ​ያ​ን​ጸ​ባ​ርቅ ያሳ​ዩ​አ​ቸው ዘንድ አላ​ቸ​ውና፥ ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲ​ህም አይ​ሞ​ቱ​ምና።

29 ከሁሉ የም​ት​በ​ልጥ ሰባ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሥር​ዐት እን​ዲህ ናት፤ በእ​ርሱ ዘንድ ይከ​ብ​ሩና ዋጋ ያገኙ ዘንድ ያላ​ቸው በሕ​ይ​ወት ሳሉ የተ​ገ​ዙ​ለ​ትን ፊቱን ያዩ ዘንድ የሚ​ቸ​ኩሉ ስለ ሆነ ሳያ​ፍሩ በብዙ ደስታ ተማ​ም​ነው በግ​ልጥ ይመ​ካ​ሉና።

30 “ከዛሬ ጀምሮ ያገኙ ዘንድ ያላ​ቸው የጻ​ድ​ቃን ነፍ​ሳት ሥር​ዐ​ታ​ቸው ይህ ነው፤ ከሓ​ድ​ያ​ንም መከራ ይቀ​በሉ ዘንድ የነ​ገ​ር​ሁህ ሥር​ዐ​ታ​ቸው፥ መን​ገ​ዳ​ቸ​ውና ፍር​ዳ​ቸው ይህ ነው።”

31 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “ከሥ​ጋዋ ከተ​ለ​የች በኋላ ይህን የነ​ገ​ር​ኸ​ኝን ታይ ዘንድ ለነ​ፍስ ቀን ይሰ​ጣ​ታ​ልን?”

32 “በእ​ነ​ዚ​ያም በሰ​ባቱ ቀኖች ይህን የነ​ገ​ር​ሁ​ህን ሥራ​ቸ​ውን ሁሉ ያዩ ዘንድ ለሰ​ባት ቀን ነጻ ናቸው፤ ከዚ​ያም በኋላ ወደ ቦታ​ቸው ይመ​ለ​ሳሉ” አለኝ።

33 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “አቤቱ ጌታዬ፥ በፊ​ትህ ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን ካገ​ኘሁ ይህ​ንም ለባ​ሪ​ያህ ዳግ​መኛ ንገ​ረው፤ በፍ​ርድ ቀን ጻድ​ቃን በል​ዑል ዘንድ ለኃ​ጥ​ኣን መለ​መን ይች​ላ​ሉን?

34 አባ​ቶ​ችም ለል​ጆ​ቻ​ቸው፥ ልጆ​ችም ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው፥ ወን​ድ​ሞ​ችም ለወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው፥ ዘመ​ዶ​ችም ለዘ​መ​ዶ​ቻ​ቸው፥ ወዳ​ጆ​ችም ለወ​ዳ​ጆ​ቻ​ቸው መለ​መን ይች​ላ​ሉን?”

35 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “በፊቴ ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን አግ​ኝ​ተ​ሃ​ልና ይህ​ንም እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፦ የፍ​ርድ ቀንስ ለአ​ንድ ጊዜ ናት፤ በሁ​ሉም ትእ​ዛዝ ላይ የእ​ው​ነት ማኅ​ተ​ምን ያሳ​ያ​ቸ​ዋል።

36 ዛሬ አባት ልጁን ስለ እርሱ፥ ልጅም አባ​ቱን፥ ጌታም አገ​ል​ጋ​ዩን፥ ወዳ​ጅም ወዳ​ጁን ስለ እርሱ ታሞ ይተኛ ዘንድ፥ በል​ቶና ጠጥ​ቶም ደስ ይለው ዘንድ፥ ይፈ​ወ​ስም ዘንድ እን​ደ​ማ​ይ​ል​ከው፥

37 እን​ደ​ዚሁ አንዱ ለሌ​ላው መለ​መን ፈጽሞ የሚ​ችል ማንም የለም፤ የራ​ሱ​ንም ሸክም በባ​ል​ን​ጀ​ራው ላይ የሚ​መ​ልስ ማንም የለም። ሁሉም ዋጋ​ውን ያገ​ኛ​ልና፥ ሥራ​ውም የየ​ራሱ ነውና።”

38 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “ቀድሞ አብ​ር​ሃም ስለ ሰዶ​ምና ገሞራ፥ ሙሴም በም​ድረ በዳ በበ​ደሉ ጊዜ ስለ አባ​ቶ​ቻ​ችን እንደ ለመነ ዛሬ እን​ዴት አገ​ኘን?

39 ኢያሱ በአ​ካን ዘመን ስለ እስ​ራ​ኤል፥ ሳሙ​ኤ​ልም በሳ​ኦል ዘመን፥

40 ዳዊ​ትም ስለ ቸነ​ፈር፥ ሰሎ​ሞ​ንም ስለ ቤተ መቅ​ደስ፥ ኤል​ያ​ስም ስለ ዝና​ምና ስለ ሙታን ይድኑ ዘንድ፥

41 ሕዝ​ቅ​ያ​ስም በሰ​ና​ክ​ሬም ዘመን ለሕ​ዝቡ፥ ብዙ ሰዎ​ችም ስለ ብዙ​ዎች ለመኑ።

42 እን​ግ​ዲህ ዛሬ መዋ​ቲው በሕ​ይ​ወት ሳለ፥ ኀጢ​አ​ትም በዝታ ሳለች ጻድ​ቃን ስለ ኃጥ​ኣን ከለ​መኑ ያን​ጊ​ዜስ እን​ደ​ዚሁ እንደ ምን አይ​ሆ​ንም?”

43 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “የዚህ የዛ​ሬው ዓለም ፍጻ​ሜው ገና አል​ሆ​ነ​ምና፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ክብር በው​ስጡ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ተገ​ልጦ የሚ​ኖር አይ​ደ​ለ​ምና-። ስለ​ዚ​ህም ጽኑ​ዓን ለድ​ኩ​ማን ለመኑ።

44 የፍ​ርድ ቀንስ የዚህ ዓለም መጨ​ረሻ ናት፤ መዋ​ቲው ያልፍ ዘንድ፥ የማ​ያ​ል​ፈ​ውም ይተካ ዘንድ፥ ለሚ​መ​ጣው ዓለም መጀ​መ​ሪያ ናት።

45 ከዚህ በኋላ ድካም ይሻ​ራል፤ ጠብም ይጠ​ፋል፤ ጽድ​ቅም ታብ​ባ​ለች፤ ቅን​ነት ትጸ​ና​ለች።

46 ያን​ጊዜ በፍ​ርድ ድል የተ​ነሣ ሰውን ይቅር ማለት የሚ​ቻ​ለው የለም፤ ድል የነ​ሣ​ው​ንም መከራ ሊያ​ጸ​ና​በት የሚ​ችል የለም።”

47 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “ቃሌ እንደ ቀደ​መው ነው፤ አሁ​ንም እን​ዲህ እላ​ለሁ፦ ምድር አዳ​ምን ባታ​ስ​ገ​ኘው በተ​ሻለ ነበር፤ ከአ​ስ​ገ​ኘ​ች​ውም እን​ዳ​ይ​በ​ድል ባስ​ተ​ማ​ረ​ችው ነበር።

48 ሁላ​ችን የም​ን​ኖ​ረው ሕይ​ወት ምን ይጠ​ቅ​መ​ናል? በኀ​ዘን እን​ኖ​ራ​ለ​ንና፤ ከሞ​ት​ንም በኋላ ዳግ​መኛ ፍርድ ይቈ​የ​ና​ልና።

49 አዳም ሆይ! ምን አደ​ረ​ግ​ንህ? አንተ ባት​በ​ድል ይህች መከራ በእኛ ላይ ባል​መ​ጣ​ች​ብን ነበር።

50 ተስፋ ያስ​ደ​ረ​ግ​ኸን፥ ሞት የሌ​ለ​በት የሚ​መ​ጣው ዓለም ምን ይጠ​ቅ​መ​ናል? እኛ ግን ሞትን የሚ​ያ​መጣ ሥራን ሠራን።

51 የነ​ገ​ሩ​ንን በጎ​ውን ተስፋ አል​ሠ​ራ​ንም፤ እኛ ግን ክፉ ሥራን ሠራን። ዐመ​ፅ​ንም ተከ​ተ​ልን።

52 ኀዘ​ንና ደዌ የሌ​ለ​ባ​ቸ​ውን፥ ለእኛ የተ​ዘ​ጋ​ጁ​ትን ቤቶች አል​ተ​ከ​ተ​ል​ንም። እኛ ግን ኀጢ​አ​ትን ሠራን።

53 ያጸ​ና​ቸው ዘንድ መከራ የተ​ቀ​በሉ ጻድ​ቃን የል​ዑ​ልን ጌት​ነት ያዩ ዘንድ አላ​ቸ​ውና፤ እኛ ግን በበ​ደ​ላ​ችን ኖርን።

54 ፍሬው የማ​ይ​ጠ​ወ​ልግ ገነት ይገ​ለ​ጣ​ልና፥ በው​ስ​ጡም የሚ​ገ​ኘው ፍሬ ደስ​ታና ሕይ​ወት ነውና።

55 እኛ ግን አን​ገ​ባም፤ የማ​ን​መ​ሰ​ገ​ን​በ​ትን ሥራ እን​ሠ​ራ​ለ​ንና።

56 ትዕ​ግ​ሥ​ትን ያጸ​ኗት ፊታ​ቸው ይበ​ራ​ልና፥ የእኛ ፊት ግን ከጨ​ለማ ይልቅ ይጠ​ቍ​ራል።

57 እነሆ፥ ከሞ​ትን በኋላ በእኛ ላይ ምን እን​ዳለ ሳና​ውቅ እን​ኖ​ራ​ለን።”

58 መል​አ​ኩም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “በዚህ ዓለም ለሚ​ጋ​ደል፥ በም​ድር ለተ​ወ​ለደ ሰው የታ​ሰ​በ​ለት ይህ ነው።

59 ድል ያደ​ረገ እኔ ያል​ሁ​ትን ያገ​ኛል፤ ድል የተ​ነሣ ግን አንተ ያል​ኸ​ውን ያገ​ኛል።

60 ትድኑ ዘንድ ሕይ​ወ​ትን ምረ​ጧት ብሎ ሙሴ ለሕ​ዝቡ የነ​ገ​ራ​ቸው መን​ገድ ይህች ናት። ነገር ግን እር​ሱን አል​ተ​ቀ​በ​ሉ​ትም፤ ከእ​ር​ሱም በኋላ ነቢ​ያ​ትን የተ​ና​ገ​ር​ኋ​ቸው እኔ​ንም አል​ተ​ቀ​በ​ሉም።

61 በሚ​ያ​ምኑ ሰዎች ደስታ እን​ዳለ በሚ​ጠ​ፉት ሰዎች ኀዘን የለም።”

62 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “አቤቱ፥ ምን​ጊ​ዜም እንደ ኢም​ንት የሆ​ኑ​ትን ይቅር ባላ​ቸው ጊዜ ልዑል ዛሬ ይቅር ባይ እን​ዲ​ባል ፈጽሜ አው​ቃ​ለሁ።

63 ይቅር ባይ ነው፤ ወደ ሕጉ የተ​መ​ለ​ሱ​ትን ይቅር ይላ​ቸ​ዋ​ልና።

64 ታጋ​ሽም ነው፤ የበ​ደ​ሉ​ትን ሰዎች እንደ ልጆች ይታ​ገ​ሣ​ቸ​ዋ​ልና።

65 ለጋ​ስም ነው፤ እንደ ሥራ​ቸው እን​ደ​ሚ​ገ​ባ​ቸው መጠን ለነ​ገ​ር​ሁህ ሰዎች ይሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ልና።

66 ምሕ​ረ​ቱም የበዛ ነው፤ ላሉት፥ ለሚ​ታ​ዘ​ዙ​ትም፥ ይመ​ሰ​ገኑ ዘንድ ላላ​ቸ​ውም ቸር​ነ​ቱን ፈጽሞ ያበ​ዛ​ልና።

67 ቸር​ነ​ቱን ፈጽሞ ካላ​በዛ ይህ ዓለም ባል​ኖረ ነበ​ርና፥ በእ​ር​ሱም ያሉ ባል​ኖሩ ነበ​ርና።

68 ለጋ​ስም ነው፤ ኃጥ​ኣን ከኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው ይመ​ለሱ ዘንድ ከቸ​ር​ነቱ ካል​ሰ​ጣ​ቸው ሰው ሁሉ ባል​ዳነ ነበ​ርና።

69 ፈራ​ጅም ነው፤ እርሱ የፈ​ጠ​ረ​ውን ፍጥ​ረት ካል​ጠ​በቀ የከ​ሓ​ድ​ያን ብዛ​ታ​ቸው ይጠ​ፋ​ልና፤ ከቍ​ጥ​ራ​ቸ​ውም ብዛት አይ​ቀ​ር​ምና። ያም ባይ​ሆን በጣም ጥቂት ነው።”

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች