Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

ተረፈ ባሮክ 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 አቤ​ሜ​ሌ​ክም ኤር​ም​ያስ ከላ​ከው ቦታ በቀ​ትር ጊዜ በለ​ሱን አመጣ፤ ጽፍቅ ያለች ዱር​ንም አገኘ፤ ጥቂ​ትም ያርፍ ዘንድ በጥ​ላዋ ስር ተቀ​መጠ፤ በለስ ያለ​ባ​ት​ንም ሙዳይ ተን​ተ​ርሶ ስድሳ ስድ​ስት ዓመት ተኛ፤ ከመ​ኝ​ታ​ውም አል​ነ​ቃም።

2 ከዚ​ያም ዘመን በኋላ ከመ​ኝ​ታው ነቅቶ ተነሣ፤ “ገና ራሴን ይከ​ብ​ደ​ኛ​ልና፥ እን​ቅ​ል​ፌ​ንም አል​ጨ​ረ​ስ​ሁ​ምና ዳግ​መኛ ጥቂት ልተኛ” አለ።

3 ያንም የበ​ለ​ሱን ሙዳይ ከፈተ፤ በለ​ሶ​ችም አዲስ ሆነው፥ ወተ​ታ​ቸ​ውም ሲፈ​ስስ አገኘ፤ ራሱ​ንም ከብ​ዶት ነበ​ርና እን​ቅ​ል​ፉ​ንም አል​ጨ​ረ​ሰ​ምና ይተኛ ዘንድ ወደደ።

4 እን​ዲ​ህም አለ፥ “ተመ​ልሼ እን​ዳ​ል​ተኛ እን​ዳ​ል​ዘ​ገ​ይም እፈ​ራ​ለሁ፤ አባቴ ኤር​ም​ያስ ተግቶ በጧት ልኮ​ኛ​ልና እን​ዳ​ይ​ቈ​ጣኝ እፈ​ራ​ለሁ።

5 ሙቀት ሆኗ​ልና፥ በሁ​ሉም የሚ​ተ​ው​በት ጊዜ የለ​ምና አሁን ተነ​ሥቼ እሄ​ዳ​ለሁ።”

6 ተነ​ሥ​ቶም የበ​ለ​ሱን ሙዳይ ይዞ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ከተማ ገባ። ከተ​ማ​ው​ንም ቤቱ​ንም አላ​ወ​ቀም።

7 ጽኑ ድን​ጋጤ መጥ​ቶ​በ​ታ​ልና “አቤቱ፥ አንተ የተ​መ​ሰ​ገ​ንህ ነህ” አለ።

8 እን​ዲ​ህም አለ፥ “ይህቺ ከተማ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም አይ​ደ​ለ​ች​ምን? በተ​ራ​ራው ጎዳና መጥ​ቻ​ለ​ሁና፥ ራሴ​ንም ከብ​ዶ​ኛ​ልና፥ እን​ቅ​ል​ፌ​ንም አል​ጨ​ረ​ስ​ሁ​ምና አእ​ም​ሮ​ዬን ዘን​ግቼ ምና​ል​ባት ተስ​ቶኝ ይሆን?

9 ከተ​ማ​ዪቱ ባዕድ እንደ ሆነ​ች​ብኝ በኤ​ር​ም​ያስ ዘንድ ይህን ነገር እን​ዴት እና​ገ​ራ​ለሁ?” ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም እንደ ሆነች በከ​ተ​ማው ያለ​ውን ምል​ክት ሁሉ ፈለገ።

10 ዳግ​መ​ኛም ወደ ከተማ ተመ​ለሰ፤ የሚ​ያ​ው​ቀ​ውም እን​ዳለ ፈለገ፤ ነገር ግን አላ​ገ​ኘም፤ “ታላቅ ድን​ጋጤ በእኔ መጥ​ቶ​ብ​ኛ​ልና አቤቱ፥ አንተ የተ​መ​ሰ​ገ​ንህ ነህ” አለ።

11 ሁለ​ተ​ኛም ከከ​ተማ ርቆ ወጣ፤ እያ​ዘ​ነም ተቀ​መጠ፤ ሲሄ​ድም አያ​ው​ቅም ነበር፤ የበ​ለ​ሱ​ንም ሙዳይ አኖረ፤ “ይህን ድን​ቁ​ርና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእኔ እስ​ኪ​ያ​ር​ቅ​ልኝ ድረስ በዚህ እቀ​መ​ጣ​ለሁ” አለ።

12 ከዚህ በኋላ ተቀ​ምጦ ሳለ አንድ ሽማ​ግሌ ሰው ከም​ድረ በዳ ሲመ​ለስ አየ።

13 አቤ​ሜ​ሌ​ክም እን​ዲህ አለ፥ “አንተ ሽማ​ግሌ፥ ይቺ ከተማ ማን ናት? ብዬ እጠ​ይ​ቅ​ሃ​ለሁ።”

14 ያም ሽማ​ግሌ፥ “ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ናት” አለው፤ “ያገ​ኘ​ሁት ሰው የለ​ምና የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ካህን ኤር​ም​ያስ ወዴት አለ? ሌዋ​ዊው ባሮ​ክና የከ​ተ​ማው ሕዝብ ሁሉስ ወዴት አሉ?” አለው፤

15 ሽማ​ግ​ሌ​ውም እን​ዲህ አለው፥ “አንተ ከዚች ከተማ አይ​ደ​ለ​ህ​ምን? ይህን ያህል ዘመን ኖረህ የእ​ር​ሱን ነገር ትጠ​ይቅ ዘንድ ኤር​ም​ያ​ስን ዛሬ ማን ዐሰ​በው?

16 ተማ​ርኮ በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር እጅ ተሰ​ጥ​ቶ​አ​ልና፤ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም ያስ​ተ​ምር ዘንድ ወደ ባቢ​ሎን ሄዶ​አ​ልና ኤር​ም​ያ​ስስ ከሕ​ዝቡ ጋር በባ​ቢ​ሎን አለ።”

17 አቤ​ሜ​ሌ​ክም ያን​ጊዜ ከዚያ ከሽ​ማ​ግ​ሌው ይህን ቃል ሰማ።

18 አቤ​ሜ​ሌ​ክም እን​ዲህ አለው፥ “ሰውን፥ ይል​ቁ​ንም ሽማ​ግ​ሌ​ውን ሰው ሊን​ቁት አይ​ገ​ባም እንጂ አንተ ሽማ​ግሌ ሰው ባት​ሆን በሰ​ደ​ብ​ሁህ ነበር፤ በአ​ን​ተም በዘ​በ​ት​ሁ​ብህ ነበር፤ ያም ባይ​ሆን አእ​ም​ሮ​ውን ያጣ ሽማ​ግሌ ብዬ በሰ​ደ​ብ​ሁህ ነበር።

19 ሕዝቡ ተማ​ር​ከው ወደ ባቢ​ሎን ሄዱ፤ ስለ​ም​ት​ለ​ውስ ነገር የሰ​ማይ ሻሻቴ እንኳ በእ​ነ​ርሱ ላይ ቢወ​ርድ ወደ ባቢ​ሎን ተማ​ር​ከው ይሄዱ ዘንድ ጊዜው አይ​ደ​ለም።

20 አንተ ግን ተማ​ር​ከው ወደ ባቢ​ሎን ሄዱ ትላ​ለህ፤ በሕ​ዝቡ ዘንድ ላሉ ለበ​ሽ​ተ​ኞች እን​ሰጥ ዘንድ አባቴ ኤር​ም​ያስ እኔን እንደ ላከኝ ጥቂት በለስ ላመጣ ወደ አግ​ሪ​ጳስ ወይን ቦታ ሄድሁ።

21 ሄጄም ከዚያ ደረ​ስሁ፤ ያዘ​ዘ​ኝ​ንም ይዤ ተመ​ለ​ስሁ፤ ስሄ​ድም አን​ዲት ዛፍ አገ​ኘሁ፤ የቀ​ትር ጊዜ ነበ​ርና በበ​ታ​ችዋ ዐርፍ ዘንድ ተቀ​መ​ጥሁ።

22 ከዚ​ያም የበ​ለ​ሱን ሙዳይ ተን​ተ​ርሼ ተኛሁ፤ ከእ​ን​ቅ​ል​ፌም በነ​ቃሁ ጊዜ የዘ​ገ​የሁ መሰ​ለኝ፤ የበ​ለ​ሱ​ንም ሙዳይ ከፍቼ አየሁ፤ መርጬ እን​ደ​ለ​ቀ​ም​ኋ​ቸው ወተቱ ሲፈ​ስስ አገ​ኘ​ሁት።

23 እነሆ፥ አንተ ሕዝቡ ተማ​ር​ከው ወደ ባቢ​ሎን ሄዱ ትላ​ለህ፤ እነሆ፥ በለሱ እን​ዳ​ል​ጠ​ወ​ለገ እይ” ብሎ የበ​ለ​ሱን ሙዳይ ከፍቶ አሳ​የው።

24 ሽማ​ግ​ሌ​ውም በለሱ አዲስ እንደ ሆነ፥ ወተ​ቱም እን​ደ​ሚ​ፈ​ስስ አየ፤ ያን​ጊ​ዜም ሽማ​ግ​ሌው አደ​ነቀ።

25 አቤ​ሜ​ሌ​ክ​ንም እን​ዲህ አለው፥ “ልጄ፥ አንተ ደግ ሰው ነህ፤ ፈጣ​ሪህ የዚ​ህ​ችን ከተማ ጥፋት ሊያ​ሳ​ይህ አል​ወ​ደ​ደ​ምና አም​ላክ ለአ​ንተ መረ​ጋ​ጋ​ትን አም​ጥቶ አድ​ኖ​ሃል።

26 እነሆ፥ ሕዝቡ ወደ ባቢ​ሎን ተማ​ር​ከው ከሄዱ ዛሬ ስድሳ ስድ​ስት ዓመት ሆነ።

27 ልጄ፥ ፈጽ​መህ ልታ​ው​ቅስ ከወ​ደ​ድህ ዘሮ​ችዋ እንደ በቀሉ ወደ እር​ሻ​ዎች ፈጽ​መህ ተመ​ል​ከት፤ የበ​ለ​ስም ጊዜው አይ​ደ​ለም፤” ያን​ጊዜ አቤ​ሜ​ሌክ የዚህ ሁሉ ጊዜው እን​ዳ​ል​ሆነ ዐወቀ።

28 ቃሉ​ንም አሰ​ምቶ፥ “የሰ​ማ​ይና የም​ድር አም​ላክ፥ በሀ​ገሩ ሁሉ ያሉ የጻ​ድ​ቃን ነፍ​ሳት ዕረ​ፍ​ታ​ቸው የሆ​ንህ ጌታ​ዬና አም​ላኬ ሆይ፥ አመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ለሁ፥” አለ።

29 ሽማ​ግ​ሌ​ው​ንም፥ “ይህ ወር ምን​ድን ነው?” አለው፤ እር​ሱም፦ የኔ​ሳን ወር ዐሥራ ሁለ​ተ​ኛው ቀን፥ ይኸ​ውም ሚያ​ዝያ ነው” አለው።

30 ከዚ​ህም በኋላ አቤ​ሜ​ሌክ ለዚህ ሽማ​ግሌ ከበ​ለ​ሶቹ ሰጠው፤ እር​ሱም፥ “አም​ላክ ወደ ሰማ​ያ​ዊት ሀገር ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ይም​ራህ” አለው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች