Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

ተረፈ ባሮክ 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 አቤ​ሜ​ሌ​ክም ተነ​ሥቶ ከከ​ተማ ወደ ውጭ ከወጣ በኋላ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጸለየ።

2 እነ​ሆም፥ መል​አክ መጥቶ ወደ ባሮክ መራው፤ በመ​ቃ​ብር ቤትም ተቀ​ምጦ አገ​ኘው።

3 ሰላ​ም​ታም በተ​ሰ​ጣጡ ጊዜ እርስ በር​ሳ​ቸው ተለ​ቃ​ቅ​ሰው ተሳ​ሳሙ፤ በሙ​ዳ​ዩም ውስጥ በለ​ሱን አይቶ ዐይ​ኖ​ቹን ወደ ሰማይ አቀና።

4 እን​ዲ​ህም ብሎ ጸለየ፤ “ለወ​ዳ​ጆቹ ለጻ​ድ​ቃን ዋጋ​ቸ​ውን የሚ​ሰ​ጣ​ቸው አም​ላክ ገናና ነው፤ ነፍሴ ሆይ፥ ተዘ​ጋጂ፤ ለቅ​ዱስ ማደ​ሪ​ያሽ ለሥጋ ይህን እየ​ነ​ገ​ርሽ ደስ ይበ​ልሽ፤ ልቅ​ሶ​ሽም ወደ ደስታ ይመ​ለ​ስ​ል​ሻል።

5 ከዚ​ያም በኋላ የታ​መ​ነው ይመ​ጣል፤ ወደ ሬሳ​ሽም ይመ​ል​ስ​ሻል፤ ድን​ግል ወደ ሆነው ወደ ሃይ​ማ​ኖ​ት​ሽም ተመ​ል​ከች።

6 እን​ደ​ም​ት​ነ​ሺም ወደ እነ​ዚህ በለ​ሶች ተመ​ል​ከች፤ ከተ​ለ​ቀሙ ስድሳ ስድ​ስት ዓመት ነው፤ አል​ደ​ረ​ቁም፤ አል​ተ​ሉ​ምም፤ ነገር ግን ወተ​ታ​ቸው እስከ ዛሬ ገና ይፈ​ስ​ሳል።

7 ኀጢ​አት የለ​ብ​ሽ​ምና፥ የበ​ለ​ሱን ሙዳይ ከጠ​በቀ ከእ​ው​ነ​ተ​ኛው መል​አ​ክም ዘንድ የታ​ዘ​ዝ​ሺ​ውን ትእ​ዛዝ ጠብ​ቀ​ሻ​ልና ሥጋዬ በአ​ንቺ እን​ዲህ ያደ​ር​ጋል፤ እር​ሱም ዳግ​መኛ በኀ​ይሉ ይጠ​ብ​ቅ​ሻል።”

8 ባሮ​ክም እን​ዲህ ብሎ ከጸ​ለየ በኋላ አቤ​ሜ​ሌክ መለሰ፤ “እኔን የሰ​ወረ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለኤ​ር​ም​ያስ ወደ ባቢ​ሎን የም​ን​ጽ​ፋ​ቸ​ውን ቃሎች ይገ​ል​ጥ​ልን ዘንድ ዳግ​መኛ ተነ​ሥ​ተህ ጸልይ” አለው።

9 ባሮ​ክም ጸለየ፤ እን​ዲ​ህም አለ፥ “ኀያል አም​ላክ፥ ብር​ሃ​ንም ከአ​ፍህ የሚ​ወጣ ጌታ ሆይ፥ እለ​ም​ንህ ዘንድ እወ​ድ​ዳ​ለሁ፤

10 ለቸ​ር​ነ​ት​ህም እገ​ዛ​ለሁ፤ ስም​ህም ገናና ነው፤ እር​ሱ​ንም መር​ምሮ ማወቅ የሚ​ቻ​ለው የለም።

11 በል​ቡ​ናዬ ፈቃ​ድ​ህን ለማ​ድ​ረግ በደ​ግ​ነት የታ​ወ​ቅሁ እሆን ዘንድ፥ ለአ​ገ​ል​ጋ​ይህ ለኤ​ር​ም​ያ​ስም ወደ ባቢ​ሎን ጽፌ እልክ ዘንድ የኔን የባ​ሪ​ያ​ህን ልመና ስማ።”

12 ይህ​ንም ሲጸ​ልይ መል​አኩ መጥቶ ለባ​ሮክ እን​ዲህ አለው፥ “ብሩህ ነገ​ርን የም​ት​መ​ክር ባሮክ ሆይ፥ አንተ ወደ ኤር​ም​ያስ ትልክ ዘንድ ማንን እል​ካ​ለሁ? ብለህ አታ​ስብ።

13 ነገ ፀሐይ ሲወጣ ንስር ወደ አንተ ይመ​ጣል፤ ወደ ኤር​ም​ያ​ስም የም​ት​ል​ከ​ውን ነገር አንተ መር​ምር፤ በመ​ጽ​ሐ​ፍም ጻፍ።”

14 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እን​ዲህ በላ​ቸው፥ “በእ​ና​ንተ ዘንድ እን​ግዳ ሰው ቢኖር እስከ ዐሥራ አም​ስት ቀን ድረስ ከእ​ና​ንተ ይለይ።

15 ከዚ​ህም በኋላ ወደ ሀገ​ራ​ችሁ አገ​ባ​ች​ኋ​ለሁ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ እስከ ዐሥራ አም​ስት ቀንም ድረስ ከባ​ቢ​ሎን ያል​ተ​ለየ ሰው ቢኖር ኤር​ም​ያስ ወደ ከተማ ገብቶ በባ​ቢ​ሎን ያሉ እስ​ራ​ኤ​ልን ይዝ​ለ​ፋ​ቸው፤ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።”

16 ይህ​ንም ከተ​ና​ገረ በኋላ መል​አኩ ከባ​ሮክ ዘንድ ሄደ። ባሮ​ክም እስከ አደ​ባ​ባዩ ድረስ ሸኘው፤ ወረ​ቀ​ትና ጥቁር ቀለ​ምም አመጣ።

17 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አገ​ል​ጋዩ ባሮክ እን​ዲህ ብሎ ደብ​ዳቤ ጻፈ፥ “ስለ ስድ​ባ​ች​ንና ስለ ጥፋ​ታ​ችን ያዘ​ንን ሆነን እን​ወጣ ዘንድ ፈጣ​ሪ​ያ​ችን አል​ተ​ወ​ን​ምና ወደ ባቢ​ሎን ለተ​ማ​ረ​ከው ለኤ​ር​ም​ያስ ደስ​ታና ሐሤት ይሁን።

18 ስለ​ዚህ ነገር ጌታ​ችን እን​ባ​ች​ንን አይቶ አዘ​ነ​ልን፤ አስ​ቀ​ድሞ ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን ለአ​ብ​ር​ሃ​ምና ለይ​ስ​ሐቅ፥ ለያ​ዕ​ቆ​ብም ያጸ​ና​ውን ቃል ኪዳን ዐሰበ።

19 መል​አ​ኩ​ንም ወደ እኔ ልኮ ወደ አንተ የላ​ክ​ሁ​ብ​ህን ነገ​ሮች ነገ​ረኝ።

20 “ከግ​ብፅ ምድ​ርና ከእ​ሳት ቤቶች ያወ​ጣን የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያደ​ረ​ጋ​ቸው ነገ​ሮች እኒህ ናቸው፤ ልቡ​ና​ች​ሁን ከፍ ከፍ አደ​ረ​ጋ​ችሁ፤ በፊ​ቱም አን​ገ​ታ​ች​ሁን አደ​ነ​ደ​ና​ችሁ እንጂ ሕጉን ሁሉ አል​ጠ​በ​ቃ​ች​ሁ​ምና።

21 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከወ​ዳጄ ከኤ​ር​ም​ያስ አፍ ቃሌን አል​ሰ​ማ​ች​ሁም ብሏ​ልና ለባ​ቢ​ሎን አገ​ዛዝ አሳ​ልፎ ሰጣ​ችሁ፤ ቃሌን የሰሙ ሰዎ​ችን ግን ከባ​ቢ​ሎን አወ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ከባ​ቢ​ሎ​ንም ወጥ​ተው በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም እን​ግዳ አይ​ሆ​ኑም።

22 መን​ገ​ዳ​ቸ​ው​ንም ልታ​ው​ቅ​ባ​ቸው ብት​ወ​ድድ በዮ​ር​ዳ​ኖስ ውኃ ፈት​ና​ቸው፤ የዚ​ህን ደብ​ዳቤ ምል​ክት ያል​ሰማ ሰው ግን የበ​ለጠ ምል​ክት ማኅ​ተም አለ።”

23 ባሮ​ክም እን​ዲህ ጽፎ ከመ​ቃ​ብር ቤት ወጣ፤ ንስ​ሩም፥ “ሃይ​ማ​ኖ​ትን የም​ታ​ስ​ተ​ምር ባሮክ ሆይ፥ ቸር አለ​ህን?” አለው።

24 ባሮ​ክም፥ “ከሰ​ማይ አዕ​ዋፍ ሁሉ የተ​መ​ረ​ጥህ ነህና፥ በዐ​ይ​ኖ​ች​ህም ብር​ሃን የታ​ወ​ቅህ ነህና ትና​ገ​ራ​ለህ።

25 አሁ​ንም በዚህ ምን ልታ​ደ​ርግ መጣህ? ንገ​ረኝ” አለው። ንስ​ሩም፥ “የወ​ደ​ድ​ኸ​ውን ሁሉ ልት​ል​ከኝ ወደ​ዚህ መጣሁ” አለው።

26 ባሮ​ክም፥ “እነ​ዚ​ህን ነገ​ሮች ለኤ​ር​ም​ያስ ወደ ባቢ​ሎን ማድ​ረስ ትች​ላ​ለ​ህን?” አለው፤ ንስ​ሩም፥ “ስለ​ዚህ ተላ​ክሁ” አለው።

27 ባሮ​ክም ደብ​ዳ​ቤ​ውን ያዘ፤ ከዚያ አቤ​ሜ​ሌክ ከሰ​ጠው ከበ​ለሱ ሙዳ​ይም ዐሥራ አም​ስ​ቱን በለስ አም​ጥቶ በን​ስሩ አን​ገት አሰረ።

28 “የአ​ዕ​ዋፍ ሁሉ ንጉ​ሣ​ቸው ንስር ሆይ፥ በሰ​ላ​ምና በደ​ኅና ሂደህ ወሬ​ያ​ቸ​ውን አም​ጣ​ልን እል​ሃ​ለሁ አለው።

29 ኖኅ የላ​ከ​ውን፥ ዳግ​መ​ኛም ወደ እርሱ መመ​ለ​ስን እንቢ ያለ​ውን ቁራ አት​ም​ሰ​ለው። ነገር ግን ለኖኅ ቃሏን ሦስት ጊዜ የመ​ለ​ሰች ርግ​ብን ምሰ​ላት።

30 እን​ደ​ዚ​ሁም ሁሉ ለአ​ንተ በጎ ነገር ይሆ​ንህ ዘንድ እኒ​ህን ያማሩ ነገ​ሮች ለኤ​ር​ም​ያ​ስና ከእ​ርሱ ጋራ ላሉ እስ​ራ​ኤል ውሰድ፤ አም​ላክ ለመ​ረ​ጣ​ቸው ወገ​ኖች ይህን ደስታ ንገ​ራ​ቸው።

31 አዕ​ዋ​ፍም ሁሉ ቢከ​ብ​ቡህ፥ ይገ​ድ​ሉ​ህም ዘንድ ወድ​ደው የጽ​ድቅ ጠላ​ቶች ሁሉ ቢከ​ብ​ቡህ ስለ እው​ነት ቀድ​መ​ሃ​ቸው ሂድ።

32 ጌታም ኀይ​ልን ይሰ​ጥ​ሃል፤ የተ​ወ​ረ​ወረ ፍላጻ ቀንቶ እን​ዲ​ሄድ አን​ተም በፈ​ጣ​ሪህ ኀይል ቀን​ተህ ሂድ እንጂ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አት​በል” አለው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች