የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

ማስታወቂያዎች

መላው መጽሐፍ ቅዱስ ብሉይ ኪዳን አዲስ ኪዳን


መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 7

1 መል​አ​ኩም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ይህ​ንስ ዓለም ልዑል ስለ ብዙ​ዎች ፈጠ​ረው፤ የሚ​መ​ጣ​ውን ግን ስለ ጥቂ​ቶች ፈጠ​ረው።

2 “ዕዝራ! እነሆ በፊ​ትህ ምሳ​ሌ​ውን እተ​ረ​ጕ​ም​ል​ሃ​ለሁ፤ ምድ​ርን ጠይ​ቃት፤ ትነ​ግ​ር​ሃ​ለ​ችም፤ ከእ​ርሱ ሸክላ የሚ​ገ​ኝ​በ​ትን መሬት ታስ​ገ​ኛ​ለ​ችና፥ መሬ​ትም ወርቅ ከእ​ርሱ የሚ​ገ​ኝ​በ​ትን ታስ​ገ​ኛ​ለ​ችና፥ ከወ​ርቅ ይልቅ ሸክላ እጅግ ይበ​ዛል።

3 የዚህ ዓለም ሥራም እን​ዲሁ ነው፤ በው​ስጡ የተ​ፈ​ጠሩ ብዙ ናቸው፤ የሚ​ድኑ ግን ጥቂ​ቶች ናቸ​ውና።”

4 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “ልብ ከጥ​በብ የተ​ነሣ ደስ ይበ​ላት፤ ጆሮም ነገ​ርን ትጠጣ።

5 ጆሮ ለመ​ስ​ማት ተሠ​ር​ት​ዋ​ልና፥ ልብም ለማ​ወቅ ተፈ​ጥ​ሯ​ልና፥ ሰው ከጥ​ቂት ሕይ​ወት በቀር ሳይ​ሰ​ጠው ባል​ወ​ደ​ደው ይሄ​ዳል።

6 አቤቱ ለባ​ሪ​ያህ ከፈ​ቀ​ድ​ህ​ለት፥ ዓለም ሰውን በሚ​ች​ለው ገን​ዘብ ሙታን ሁሉ መኖ​ርን ይችሉ ዘንድ እን​ዲ​ያ​ፈ​ራ​ልን እና​ር​ስና እን​ዘራ ዘንድ ልብ​ንና ሕሊ​ናን ብት​ሰ​ጠን በተ​ሻ​ለን ነበር።

7 የእ​ጆ​ችህ ፍጥ​ረት እኛ አንተ እን​ደ​ተ​ና​ገ​ርህ ሁላ​ችን የተ​ካ​ከ​ልን ነንና።

8 ዛሬ በማ​ኅ​ፀን ትፈ​ጥ​ረ​ዋ​ለ​ህና፥ ሥጋ​ንና ሕዋ​ሳ​ት​ንም ትቀ​ር​ጽ​ለ​ታ​ለ​ህና፥ ማስ​ተ​ዋ​ል​ንም ትሰ​ጠ​ዋ​ለ​ህና፥ በእ​ሳ​ትና በውኃ ትጠ​ብ​ቀ​ዋ​ለ​ህና፥ ያን የፈ​ጠ​ር​ኸ​ው​ንም በማ​ኅ​ፀን ዘጠኝ ወር ትሸ​ከ​መ​ዋ​ለ​ህና፥ ባን​ተም ቃል ይጠ​በ​ቃ​ልና።

9 ዳግ​መ​ኛም እናቱ በወ​ለ​ደ​ችው ጊዜ፥ ከተ​ወ​ለ​ደና ከተ​ፈ​ጠረ በኋላ፥ የሚ​ጠ​ባ​በ​ትን ወራት እስ​ኪ​ጨ​ርስ ድረስ ይህ ባሪ​ያህ ሕፃኑ ያድግ ዘንድ፥

10 ከሰ​ው​ነ​ትዋ በላይ ካሉ ከጡ​ቶ​ች​ዋም የጡት ፍሬ ወተት ይፈ​ስ​ለት ዘንድ ታዝ​ለ​ታ​ለህ፥

11 ይህ ባሪ​ያህ እስከ ጊዜው ድረስ ያድግ ዘንድ በቸ​ር​ነ​ትህ ታሳ​ድ​ገ​ዋ​ለህ።

12 በቸ​ር​ነ​ት​ህም ትመ​ግ​በ​ዋ​ለህ፤ ሕግ​ህ​ንም ታስ​ተ​ም​ረ​ዋ​ለህ፤ በጥ​በ​ብ​ህም ትገ​ሥ​ጸ​ዋ​ለህ።

13 ከዚህ በኋላ የፈ​ጠ​ር​ኸ​ው​ንና ሕያው ያደ​ረ​ግ​ኸ​ውን ያን ባሪ​ያ​ህን ትገ​ድ​ለ​ዋ​ለህ።

14 ፈጥ​ረህ ይህን ያህል ዘመን ያኖ​ር​ኸ​ውን ያን ባሪ​ያ​ህን የም​ታ​ጠ​ፋው ከሆነ እን​ግ​ዲያ ለምን ፈጠ​ር​ኸው?

15 አሁ​ንም ነገ​ርህ እው​ነት ነው፤ ስለ ሁሉም አንተ ታው​ቃ​ለህ፤ ነገር ግን እና​ገር ዘንድ እኔን ያተ​ጋኝ አይ​ደ​ለም።

16 ይህን የማ​ዝን ስለ ወገ​ኖ​ች​ህና ስለ ርስ​ትህ ነው እንጂ።

17 ይህ​ንም በፊ​ትህ እማ​ልድ ዘንድ የጀ​መ​ር​ሁት ስለ እኔም፥ ስለ እነ​ዚ​ያም ነው። የሚ​መ​ጣ​ውን ዓለም ሕጉን እየ​ሰ​ማን የም​ን​ኖር የእ​ኛን መሰ​ነ​ካ​ከል አያ​ለ​ሁና።

18 ስለ​ዚ​ህም ቃሌን ስማ፤ በፊ​ትህ የም​ና​ገ​ረ​ው​ንም ልመ​ና​ዬን አድ​ም​ጥ​ልኝ።”

የዕ​ዝራ ጸሎት

19 ሳይ​ወ​ስ​ዱት የዕ​ዝራ የጸ​ሎቱ ቃል መጀ​መ​ሪያ ይህ ነው።

20 “ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ የም​ት​ኖር አቤቱ፥ በል​ዑል አር​ያም ሁነህ የም​ታይ፥ በሰ​ማይ ያለህ፥

21 ሥል​ጣ​ንህ የማ​ይ​ሸ​ነፍ፥ መን​ግ​ሥ​ትህ የማ​ያ​ልፍ፥ ሠራ​ዊተ መላ​እ​ክት በፍ​ር​ሀት የሚ​ቆ​ሙ​ልህ፥

22 ነፋ​ስና እሳት በት​እ​ዛ​ዝህ የተ​ፈ​ጠሩ፥ ቃልህ ጽኑ የሆነ፥ የተ​ና​ገ​ር​ኸ​ውም ጸንቶ የሚ​ኖር፥

23 ሥር​ዐ​ትህ ጽኑ የሆነ፥ ትእ​ዛ​ዝ​ህም የሚ​ያ​ስ​ፈራ፥ ትእ​ዛ​ዝ​ህም ጥል​ቆ​ችን የሚ​ያ​ደ​ርቅ፥ ቍጣ​ህም ተራ​ራ​ዎ​ችን የሚ​ያ​ቀ​ልጥ፤ ሕግ​ህም እው​ነት የሆነ፥

24 አቤቱ፥ የባ​ሪ​ያ​ህን ቃል ስማ፤ የባ​ሪ​ያ​ህን ልመና አድ​ምጥ፤ ነገ​ሬ​ንም አድ​ምጥ።

25 እኔ በሕ​ይ​ወት ሳለሁ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ ልቡ​ና​ዬም እን​ዳ​ሰበ መጠን እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ እመ​ል​ስ​ል​ሃ​ለ​ሁም።

26 የወ​ገ​ኖ​ች​ህን በደል አት​መ​ል​ከት፤ ለአ​ንተ የተ​ገ​ዙ​ል​ህን ጽድ​ቃ​ቸ​ውን ተመ​ል​ከት እንጂ።

27 የኃ​ጥ​ኣ​ንን ሥራ​ቸ​ውን አት​መ​ል​ከት፤ በመ​ከ​ራ​ቸው ሥር​ዐ​ትን የጠ​በ​ቁ​ትን ተመ​ል​ከት እንጂ።

28 በፊ​ትህ ክፉ ሥራን ስለ​ሠሩ አት​ቈጣ፤ በፍ​ጹም ልባ​ቸው በሕ​ግህ የታ​መ​ኑ​ትን አስብ እንጂ።

29 በሥ​ራ​ቸው እንደ እን​ስሳ የሆኑ ሰዎ​ችን ጥፋት አት​ው​ደድ። ሥር​ዐ​ት​ህን በብ​ሩህ ልቡና ያጸ​ኗ​ትን አስ​ባ​ቸው፤ ተመ​ል​ከ​ታ​ቸ​ውም እንጂ።

30 ከአ​ራ​ዊት የከፉ ሰዎ​ችን አት​ቈ​ጣ​ቸው። በጌ​ት​ነ​ትህ መታ​መን ያዘ​ወ​ተ​ሩ​ትን ውደ​ዳ​ቸው እንጂ።

31 ነገር ግን እኛና ከእኛ አስ​ቀ​ድሞ የነ​በሩ ሞትን የሚ​ያ​መጣ ሥራን ሠራን።

32 አንተ ግን ስለ እኛ፥ ስለ በደሉ ሰዎ​ችም ይቅር ባይ ሁን፤ በጎ ሥራ የሌ​ለን እኛን ይቅር ብት​ለን ያን​ጊዜ ይቅር ባይ ትባ​ላ​ላ​ህና።

33 በአ​ንተ የተ​ዘ​ጋጀ በጎ ሥራ ያላ​ቸው ጻድ​ቃ​ንን ግን በሥ​ራ​ቸው ይቅር ትላ​ቸ​ዋ​ለህ።

34 ትቈ​ጣው ዘንድ ሰው ምን​ድን ነው? ስለ እር​ሱስ ታዝን ዘንድ የመ​ዋቲ ወገን ምን​ድን ነው?

35 አሁ​ንም ከተ​ወ​ለ​ደው ወገን የማ​ይ​በ​ድል እን​ደ​ሌለ እው​ነት እና​ገ​ራ​ለሁ።

36 ነገር ግን ጌታ ሆይ፥ ስለ​ዚህ በጎ ሥራ የሌ​ላ​ቸ​ውን ይቅር ብት​ላ​ቸው ቸር​ነ​ትህ ፈጽሞ ይታ​ወ​ቃል።”

37 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “በእኔ ዘንድ እው​ነ​ትን ተና​ገ​ርህ፤ አንተ እንደ ተና​ገ​ር​ኸው እን​ዲሁ ነው።

38 ለሚ​በ​ድሉ ሰዎች ሞትን፥ ፍር​ድ​ንም፥ ጥፋ​ት​ንም በእ​ው​ነት አል​ወ​ድ​ላ​ቸ​ውም።

39 ነገር ግን ስለ ጻድ​ቃን ደስ ይለ​ኛል፤ የሚ​ድኑ ዋጋ​ቸ​ውን ያገ​ኛ​ሉና።

40 እንደ ተና​ገ​ር​ኸ​ውም እን​ዲሁ ይሆ​ናል።

41 ገበሬ ብዙ ዘር እን​ደ​ሚ​ዘራ፥ ብዙ ተክ​ል​ንም እን​ደ​ሚ​ተ​ክል፥ ጊዜ​ውም ቢሆን ዘሩ ሁሉ የሚ​በ​ቅል እንደ አይ​ደለ፥ ተክ​ሉም ሁሉ ሥር የሚ​ሰ​ድድ እንደ አይ​ደለ፥ በዚህ ዓለም ያሉ ሰዎ​ችም እን​ዲሁ ናቸው፤ ሁሉም የሚ​ድኑ አይ​ደ​ሉም።”

42 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “በፊ​ትህ ባለ​ሟ​ል​ነ​ት​ንስ ካገ​ኘሁ ልና​ገር።

43 የገ​በሬ ዘርስ ባይ​በ​ቅል ምና​ል​ባት ዝናም ባያ​ገኝ ይሆ​ናል፤ ስለ​ዚ​ህም ይጠ​ፋል።

44 ነገር ግን በእ​ጅህ የፈ​ጠ​ር​ኸው፥ በአ​ም​ሳ​ል​ህም የመ​ሰ​ል​ኸው ሰው አም​ሳ​ልህ ነውና፥ ስለ እር​ሱም ሁሉን ፈጥ​ረ​ሃ​ልና፥ እን​ግ​ዲህ እንደ ገበሬ ዘር ለምን ታደ​ር​ገ​ዋ​ለህ?

45 አቤቱ አገ​ባ​ብ​ህም አይ​ደ​ለም፤ ለወ​ገ​ኖ​ችህ ራራ፤ ርስ​ት​ህ​ንም ይቅር በል እንጂ፤ ፍጥ​ረ​ት​ህን ይቅር ትለ​ዋ​ለ​ህና።”

46 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “በዚህ ዓለም ያለው በዚህ ዓለም ላሉት ምሳ​ሌ​ያ​ቸው ነው፤ የወ​ዲ​ያው ዓለም ግን በወ​ዲ​ያው ዓለም ለሚ​ኖሩ ምሳ​ሌ​ያ​ቸው ነው።

47 ነገር ግን ዕው​ቀት ያነ​ሰህ አንተ ከእኔ ይልቅ ፍጥ​ረ​ቴን ፈጽ​መህ ትወ​ድድ ዘንድ፥ ይል​ቁ​ንም አንተ ኃጥእ ሳት​ሆን በብዙ ወገን ኃጥ​እን ትመ​ስ​ላ​ለህ።

48 ነገር ግን ስለ​ዚህ በል​ዑል ዘንድ ትመ​ሰ​ገ​ና​ለህ፤

49 ራስ​ህን አዋ​ር​ደ​ሃ​ልና፥ ፈጽ​መ​ህም ትመ​ሰ​ገን ዘንድ እን​ደ​ሚ​ገ​ባህ ራስ​ህን እንደ ጻድ​ቃን አላ​ደ​ረ​ግ​ህ​ምና።

50 አሁ​ንም በዚህ ዓለም የሚ​ኖሩ ጐስ​ቋ​ሎች በኋላ ዘመን ብዙ መከ​ራን ይቀ​በ​ላሉ። በብዙ ትዕ​ቢት ኖረ​ዋ​ልና።

51 አንተ ግን ለራ​ስህ ዕወቅ፤ እንደ አንተ ያሉ​ት​ንም ክብር መር​ምር፤

52 ገነት ለእ​ና​ንተ ተከ​ፍ​ታ​ለ​ችና፥ ዕፀ ሕይ​ወ​ትም ተተ​ክ​ሏ​ልና፥ የሚ​መ​ጣ​ውም ዓለም ተዘ​ጋ​ጅቶ ተሠ​ር​ት​ዋ​ልና፥ ደስ​ታም ተሠ​ር​ታ​ለ​ችና፥ ዕረ​ፍ​ትም ተነ​ጥ​ፋ​ለ​ችና፥ በጎ በረ​ከ​ትም ጸን​ታ​ለ​ችና፥ የጥ​በብ ሥርዋ ተገ​ኝ​ት​ዋ​ልና።

53 እን​ግ​ዲህ ወዲህ ደዌ አበቃ፤ ሞትም ጠፋ፤ መቃ​ብ​ርም ተሰ​ወ​ረች፤ ሙስ​ናም ጠፋ።

54 መከ​ራም ተዘ​ነጋ፤ የሕ​ይ​ወት መዝ​ገ​ብም ተገ​ለጠ።

55 እን​ግ​ዲህ ወዲህ ስለ​ሚ​ጠ​ፉት ሰዎች ብዛት መመ​ራ​መ​ርን አት​ድ​ገም።

56 እነ​ርሱ ነጻ​ነ​ትን አግ​ኝ​ተው ልዑ​ልን ንቀ​ው​ታ​ልና፥ ሕጉ​ንም አቃ​ል​ለ​ዋ​ልና፥ ሥር​ዐ​ቱ​ንም ትተ​ዋ​ልና።

57 ጻድ​ቃ​ኑ​ንም ረግ​ጠ​ዋ​ቸ​ዋ​ልና።

58 እን​ደ​ሚ​ሞ​ቱም እያ​ወቁ በል​ቡ​ና​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አን​ፈ​ል​ገ​ውም ብለ​ዋ​ልና።

59 ስለ​ዚ​ህም ይህ በጎው ለእ​ና​ንተ እንደ ሆነ እን​ዲ​ሁም ይህ ጥፋት ለእ​ነ​ርሱ ነው።

60 እነ​ርሱ ከተ​ፈ​ጠሩ በኋላ የፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸ​ውን ስም አሳ​ድ​ፈ​ው​ታ​ልና፥ ያዘ​ጋ​ጀ​ላ​ቸ​ውን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አላ​መ​ሰ​ገ​ኑ​ት​ምና።

61 አሁ​ንም ፍር​ዳ​ቸው ይደ​ር​ስ​ባ​ቸ​ዋል።

62 ለአ​ን​ተና እንደ አንተ ለአሉ ለጥ​ቂ​ቶች እንጂ ይህን ለብ​ዙ​ዎች አል​ተ​ና​ገ​ር​ሁም።”

63 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “አቤቱ! እነሆ፥ እስ​ካ​ሁን ድረስ በኋላ ዘመን ታደ​ር​ገው ዘንድ ያለ​ህን ብዙ ምል​ክት ነገ​ር​ኸኝ፤ ነገር ግን ጊዜው መቼ እንደ ሆነ አል​ነ​ገ​ር​ኸ​ኝም።”