Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 መል​አ​ኩም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “አንተ ራስህ ገም​ግ​መው፤ እኔ ከነ​ገ​ር​ሁህ ምል​ክት ያለፈ ብታይ፥

2 ልዑል የፈ​ጠ​ረ​ውን ዓለም ይጐ​በ​ኝ​በት ዘንድ ያለው ጊዜ እንደ ደረሰ ያን​ጊዜ ዕወቅ።

3 በዓ​ለም በየ​ሀ​ገሩ ሽብር በሆነ ጊዜ፥ አሕ​ዛ​ብም በታ​ወኩ ጊዜ፥ ሕዝ​ቡም በተ​ሸ​በሩ ጊዜ፥ አለ​ቆ​ችም በተ​ዋጉ ጊዜ፥ መሳ​ፍ​ን​ቱም በደ​ነ​ገጡ ጊዜ፥

4 ስለ​ዚህ ልዑል ከጊ​ዜው አስ​ቀ​ድሞ እንደ ተና​ገረ ያን​ጊዜ ዕወቅ።

5 በዓ​ለም የሆ​ነው ሁሉ አስ​ቀ​ድሞ በቃል፥ ኋላም በመ​ገ​ለጥ እንደ ሆነ፥

6 እን​ዲ​ሁም የል​ዑል ዓለም መጀ​መ​ሪያ በቃል፥ በተ​አ​ም​ርና በኀ​ይል፥ ኋላ ግን በሥ​ራና በድ​ንቅ ነው።

7 በም​ግ​ባ​ሩና በአ​መ​ነ​በት ሃይ​ማ​ኖቱ የዳ​ነና ማም​ለጥ የቻለ፥

8 ከነ​ገ​ር​ሁህ ሥቃይ የሚ​ድን እርሱ ብቻ ነው፤ ከዚህ ዓለም ለእኔ በለ​የ​ኋት በም​ድ​ሬና በድ​ን​በ​ሬም ሕይ​ወ​ትን ያያል።

9 ዛሬ ትእ​ዛ​ዜን ቸል ያሉ ያን​ጊዜ መከ​ራን ይቀ​በ​ላሉ፤ እኔን መፍ​ራ​ትን የተ​ዉና የና​ቁ​ኝም በገ​ሃ​ነም ውስጥ ይጨ​ነ​ቃሉ።

10 እኔ እየ​ረ​ዳ​ኋ​ቸው በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸው ሳሉ የማ​ያ​ው​ቁ​ኝም ሁሉ፥

11 እነ​ርሱ ነጻ ሳሉ በሕጌ ላይ የታ​በ​ዩም ሁሉ፥

12 የት​ዕ​ግ​ሥ​ቴም ቦታ ክፍት ሆኖ​ላ​ቸው ሳለ ልብ ያላ​ደ​ረ​ጉኝ፥ የና​ቁ​ኝም ሁሉ፥ ከሞቱ በኋላ ያው​ቁኝ ዘንድ አላ​ቸው።

13 አንተ ግን ኃጥ​ኣን እን​ዴት እን​ደ​ሚ​ፈ​ረ​ድ​ባ​ቸው አት​መ​ር​ምር፤ ጻድ​ቃን በዓ​ለ​ማ​ቸው እን​ዴት እን​ደ​ሚ​ድኑ መር​ምር እንጂ፤ የሚ​መ​ጣው ዓለም ስለ እነ​ርሱ ነውና።”

14 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አል​ሁት፦

15 “ዝናም ከካ​ፊያ እን​ደ​ሚ​በዛ ከሚ​ድ​ኑት ኋለ​ኞች ይልቅ የሚ​ጠ​ፉት እን​ደ​ሚ​በዙ ቀድሞ ተና​ገ​ርሁ፤ ዛሬም እና​ገ​ራ​ለሁ።”

16 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ዘሩ በእ​ር​ሻው መጠን እንደ ሆነ ፍር​ዱም እንደ ሥራው ነው፤ አጫ​ጁም በአ​ራሹ መጠን ነው።

17 ዛሬ በው​ስጡ የሚ​ኖ​ሩ​በት ዓለ​ማ​ቸው ሳይ​ፈ​ጠር ያዘ​ጋ​ጀ​ሁት ዓለም በጊ​ዜው ነውና።

18 ያን​ጊ​ዜም የተ​ከ​ራ​ከ​ረኝ የለም፤ ማንም የነ​በረ የለ​ምና።

19 አሁ​ንም በም​ግ​ብና ፍለጋ በሌ​ለው በዘ​ለ​ዓ​ለ​ማዊ ሕግ በተ​ዘ​ጋ​ጀው ዓለም ከተ​ፈ​ጠሩ በኋላ በሥ​ራ​ቸው ሞት ነበር።

20 ዓለ​ሙ​ንም ባየ​ሁት ጊዜ እነሆ፥ እነ​ርሱ ጠፉ። በም​ድር በተ​ዘ​ራው ሥራ​ቸ​ውም እነሆ፥ ዓለም ይጨ​ነ​ቃል።

21 ሄጄም ለጥ​ቂ​ቶቹ ራራ​ሁ​ላ​ቸው፤ ከዘ​ለ​ላ​ውም ውስጥ ፍሬ​ዎ​ችን ለእኔ አስ​ቀ​ረሁ። ከብዙ ዛፍም አንድ ተክል መረ​ጥሁ።

22 በከ​ንቱ የተ​ወ​ለዱ ብዛ​ታ​ቸው ይጠ​ፋል፤ በብዙ ሥራ የጸ​ናች ፍሬ​ዬም፥ ተክ​ሌም ትጠ​በ​ቃ​ለች።

23 አንተ ግን ዳግ​መኛ ሰባት ቀን ብት​ጾ​ምና ብት​ጸ​ልይ፥

24 ግንብ ወደ​አ​ል​ተ​ሠ​ራ​ባት ምድረ በዳ ብት​ሄ​ድና ከእ​ን​ጨት ፍሬ ብቻ ብት​በላ፥ ሥጋም ባት​በላ፥ ከእ​ን​ጨቱ ፍሬ ብቻ በቀ​ርም ወይን ባት​ጠጣ፥

25 ወደ ልዑል ሁል​ጊዜ ብት​ጸ​ልይ መጥቼ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ።”


አራ​ተ​ኛው ራእይ

26 ከዚህ በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ዘ​ዘኝ ስሙ አር​ፋድ ወደ​ሚ​ባል ምድረ በዳ ሄድሁ።

27 በሣር ውስጥ ተቀ​መ​ጥሁ፤ የም​ድረ በዳ​ንም ፍሬ ተመ​ገ​ብሁ፤ የበ​ላ​ሁ​ትም ያጠ​ግ​በኝ ነበር።

28 ከዚ​ህም ከሰ​ባ​ተ​ኛው ቀን በኋላ በሣር ውስጥ ተኝቼ ሳለሁ ልቤ እንደ ቀድ​ሞው ታወ​ከ​ብኝ።

29 አን​ደ​በ​ቴ​ንም አቅ​ንቼ በል​ዑል ፊት እና​ገር ጀመ​ርሁ፤

30 እን​ዲ​ህም አልሁ፥ “አቤቱ ጌታዬ፥ ዛፍና ሣር በሌ​ሉ​በት ምድረ በዳ ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን ፈጽ​መህ ታየ​ሃ​ቸው።

31 እን​ዲ​ህም አል​ሃ​ቸው፦ ‘አንተ እስ​ራ​ኤል ስማኝ፤ ቃሌ​ንም አድ​ም​ጠኝ፤

32 እነ​ሆም እኔ ሕጌን በው​ስ​ጣ​ችሁ እዘ​ራ​ለ​ሁና፥ በላ​ያ​ች​ሁም ፍሬን ያፈ​ራ​ልና፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም ትከ​ብ​ሩ​በ​ታ​ላ​ቸ​ሁና።’

33 አባ​ቶ​ቻ​ች​ንም ሕግ​ህን ተቀ​ብ​ለው አል​ጠ​በ​ቁም፤ በሥ​ር​ዐ​ት​ህም አል​ጸ​ኑም፤ የሕ​ግህ ፍሬ ግን አል​ጠ​ፋም፤ የአ​ንተ ገን​ዘብ ስለ​ሆነ ይጠፋ ዘንድ አይ​ቻ​ል​ምና።

34 ሕግ ያንተ ገን​ዘብ ስለ​ሆ​ነች በው​ስ​ጣ​ቸው የተ​ዘ​ራ​ውን ተግ​ባ​ራ​ቸ​ውን አል​ጠ​በ​ቁ​ምና ሕግ​ህን ተቀ​ብ​ለው ያል​ጠ​በቁ ጠፉ።

35 ምድ​ርም ዘርን ከተ​ቀ​በ​ለች በኋላ፥ ባሕ​ርም መር​ከብ በው​ስጧ ከገባ በኋላ፥ ዕቃም በው​ስጡ መብ​ልና መጠ​ጥን ከጨ​መ​ሩ​በት በኋላ፥

36 ያን​ጊዜ የዚያ የዘሩ፥ የዚ​ያም የመ​ር​ከቡ፥ የዚ​ያም የመ​ብ​ሉና የመ​ጠጡ ይጠፋ ዘንድ ጊዜው ቢሆን እን​ደ​ዚሁ የሚ​ጠፋ ይሆ​ናል። ነገር ግን የያ​ዙት ይቀ​ራሉ። ለእ​ኛስ እን​ደ​ዚሁ አይ​ደ​ለም። ሕግን ተቀ​ብ​ለን የበ​ደ​ልን እኛ እን​ጠ​ፋ​ለ​ንና፥ የተ​ቀ​በ​ለው ልባ​ች​ንም እን​ዲሁ ነው፤ ሕጉ ግን በክ​ብሩ ይኖ​ራል እንጂ አይ​ጠ​ፋም።”


ስለ​ም​ታ​ለ​ቅ​ሰው ሴት የዕ​ዝራ ራእይ

37 በዐ​ይ​ኖ​ችም በተ​መ​ለ​ከ​ትሁ ጊዜ በቀኝ በኩል እነሆ፥ አን​ዲት የም​ታ​ለ​ቅስ ሴትን አየሁ፤ በታ​ላቅ ድም​ፅም ትጮኽ ነበር፤ እጅ​ግም አዝና ነበር፤ ልብ​ሷም ተቀ​ድዶ ነበር፤ በራ​ሷም ላይ ዐመድ ነስ​ንሳ ነበር።

38 ያ ቀድሞ የማ​ስ​በው አሳ​ቤም ተለ​የኝ፤ ወደ እር​ሷም ተመ​ልሼ፥ “ምን ያስ​ለ​ቅ​ስ​ሻል? ልቡ​ና​ሽ​ንስ ለምን ታሳ​ዝ​ኛ​ለሽ? አል​ኋት።”

39 እር​ስ​ዋም አለ​ችኝ፥ “ጌታዬ ለራሴ አለ​ቅስ ዘንድ በመ​ከ​ራ​ዬም ላይ መከ​ራን እጨ​ምር ዘንድ ተወኝ፤ ፈጽሜ እኔ አዝ​ኛ​ለ​ሁና፥ ልቡ​ና​ዬም ተጨ​ን​ቃ​ለ​ችና።”

40 እኔም፥ “ምን ሆነ​ሻል? ንገ​ሪኝ” አል​ኋት።

41 እር​ስ​ዋም አለ​ችኝ፥ “እኔ ባሪ​ያህ ከጥ​ንት ጀምሮ መካን ነበ​ርሁ፤ ሠላሳ ዘመን ከባሌ ጋር ስኖር ልጅ አል​ወ​ለ​ድ​ሁም።

42 እኔም በዚያ በሠ​ላ​ሳው ዘመን ሁል​ጊዜ በየ​ጊ​ዜ​ውና በየ​ሰ​ዓቱ በመ​ዓ​ል​ትና በሌ​ሊት ወደ ልዑል እጸ​ልይ ነበር።

43 ከዚ​ህም ከሠ​ላሳ ዓመት በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የባ​ሪ​ያ​ውን ልመና ሰማ፤ መከ​ራ​ዬ​ንም አየ፤ ድካ​ሜ​ንና ሥቃ​ዬን ተመ​ል​ክቶ አንድ ልጅ ሰጠኝ፤ በእ​ር​ሱም ፈጽሞ ደስ አለኝ፤ እኔም፥ ባሌም፥ ያገ​ሬም ሰዎች ሁሉ ደስ አለን፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አመ​ሰ​ገ​ን​ነው።

44 በብዙ ድካ​ምም አሳ​ደ​ግ​ሁት።

45 ከዚ​ህም በኋላ አካለ መጠን ባደ​ረሰ ጊዜ ሚስት አጋ​ባ​ሁት፤ ሰር​ግ​ንም ሰረ​ግ​ሁ​ለት።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች