Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ስድ​ስ​ተኛ ራእይ

1 ከዚ​ህም ከሰ​ባ​ተ​ኛው ቀን በኋላ በሌ​ሊት ሕል​ምን አየሁ።

2 እነሆ፥ ጽኑ ነፋስ ከባ​ሕር ሲወጣ አየሁ፤ ማዕ​በ​ሎ​ቹም ሁሉ ታወኩ።

3 ያም ነፋስ በሰው አም​ሳል ከባ​ሕሩ ሲወጣ አየሁ፤ ከዚህ በኋላ ያ ሰው ከሰ​ማይ ደመ​ና​ዎች ጋር ወጣ፤ ፊቱ​ንም መልሶ ባየ ጊዜ፥ ሁሉ በጊ​ዜው ጊዜ ወደ እርሱ ይመ​ጣል።

4 ቃሉም በወጣ ጊዜ ከቃሉ የተ​ነሣ ሁሉ ይቀ​ል​ጣል፤ ቃሉን የሰ​ሙት ሁሉም አደሮ ማር ወደ እሳት በቀ​ረበ ጊዜ እን​ደ​ሚ​ቀ​ልጥ ይቀ​ል​ጣሉ።

5 ከዚህ በኋላ ቍጥር የሌ​ላ​ቸው ብዙ ሰዎች ከባ​ሕር የወጣ ይኽን ሰው ይዋ​ጉት ዘንድ ከአ​ራቱ ማዕ​ዘን ሲሰ​በ​ሰቡ አየሁ።

6 ከዚህ በኋ​ላም ታላቅ ተራ​ራን ሠራ፤ በላ​ዩም ተቀ​መጠ።

7 ያ ተራ​ራም የተ​ሠ​ራ​በ​ትን ላውቅ ወደ​ድሁ፤ ነገር ግን አል​ቻ​ል​ሁም።

8 ከዚ​ህም በኋላ ይጣ​ሉት ዘንድ የተ​ሰ​በ​ሰ​ቡት ሁሉ ፈጽ​መው ፈሩት። ነገር ግን ይዋ​ጉት ዘንድ ደፈሩ።

9 ከዚ​ህም በኋላ በከ​በ​ቡት ጊዜ፥ ወደ እር​ሱም በመጡ ጊዜ እጁን በእ​ነ​ርሱ ላይ አላ​ነ​ሣም፤ ጦርን ወይም ማና​ቸ​ው​ንም የጦር መሣ​ሪያ አላ​ነ​ሣም።

10 ከአፉ የእ​ሳት ማዕ​በ​ልን፥ ከከ​ን​ፈ​ሩም የእ​ሳት ነበ​ል​ባ​ልን፥ ከአ​ን​ደ​በ​ቱም የእ​ሳት ፍምን እንደ ጥቅል ነፋስ አወጣ እንጂ፤ ያ የእ​ሳት ማዕ​በል፥ ያም የእ​ሳት ነበ​ል​ባል፥ ያም የእ​ሳት ፍም ሁሉ ተቀ​ላ​ቅሎ እንደ ጥቅል ነፋስ ሆነ።

11 ሊገ​ድ​ሉት በከ​በ​ቡት በእ​ነ​ዚያ በብ​ዙ​ዎች ላይም ወረደ፤ ከዐ​መ​ዳ​ቸው ትቢ​ያና ከቃ​ጠ​ሏ​ቸው ጢስ በቀር ከእ​ነ​ርሱ የተ​ረፈ እስ​ከ​ማ​ይ​ኖር ድረስ ሁሉ​ንም አቃ​ጠ​ላ​ቸው። ከዚ​ህም በኋላ ደን​ግጬ ነቃሁ።

12 ከዚ​ህም በኋላ ያን ሰው ከዚሁ ተራራ ሲወ​ርድ አየ​ሁት፤ ለእ​ርሱ የሚ​ስ​ማሙ ብዙ​ዎች ሌሎ​ች​ንም ወደ እርሱ ጠራ።

13 ብዙ ሰዎ​ችም ወደ እርሱ መጡ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ደስ ያላ​ቸው ነበሩ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ያዘኑ ነበሩ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም እስ​ረ​ኞች ነበሩ። ከዚህ በኋላ ይህ ሁሉ በደ​ረ​ሰ​ብኝ ጊዜ ደን​ግጬ ነቃሁ፤ ወደ ልዑ​ልም ጸለ​ይሁ።

14 እን​ዲ​ህም አልሁ፥ “ቀድሞ አንተ ይህን ጌት​ነ​ት​ህን ለባ​ሪ​ያህ አሳ​የ​ኸው፤ ጸሎ​ቴ​ንም ትሰማ ዘንድ አደ​ረ​ግ​ህ​ልኝ።

15 አሁ​ንም የዚ​ህን የሕ​ል​ሜን ትር​ጓሜ ዳግ​መኛ ንገ​ረኝ።

16 ነገር ግን እኔስ እን​ደ​ም​ጠ​ራ​ጠ​ረው በእ​ነ​ዚያ ወራ​ቶች ለሚ​ኖሩ ሰዎች ወዮ​ላ​ቸው! ይል​ቁ​ንም ላል​ነ​በ​ሩት ወዮ​ላ​ቸው!

17 በኋላ ዘመን የሚ​ቈ​ያ​ቸ​ውን ገና ያል​ደ​ረ​ሰ​ላ​ቸ​ውን ባለ​ማ​ወቅ ያዝ​ና​ሉና።

18 ላሉት ግን ፈጽ​መው ስላ​ወ​ቁት ነው።

19 ስለ​ዚ​ህም ወዮ​ላ​ቸው! በዚህ ሕልም እን​ዳ​የሁ ታላቅ ጭን​ቅ​ንና ብዙ ድካ​ምን ያያ​ሉና።

20 ነገር ግን ይህ ሳይ​ደ​ርስ መከራ መቀ​በል ይሻ​ላል፤ እንደ ደመ​ናም ከዚህ ዓለም ያልፉ ዘንድ ይሻ​ላል፤ በኋላ ዘመን የም​ታ​ገ​ኛ​ቸ​ውን አያ​ው​ቁ​ምና።”


የራ​እዩ ትር​ጓሜ

21 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “የዚ​ህን የሕ​ል​ም​ህን ትር​ጓሜ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ ይህን ያል​ኸ​ኝ​ንም እተ​ረ​ጕ​ም​ል​ሃ​ለሁ።

22 ስለ​ሚ​ቀ​ሩ​ትና ስለ​ሚ​ኖ​ሩት ተና​ግ​ረ​ሃ​ልና ትር​ጓ​ሜው እን​ዲህ ነው።

23 በእ​ነ​ዚያ ወራ​ቶች ያን መከራ የሚ​ያ​ዩት እነ​ዚያ የሚ​ቀ​ሩት ናቸው፤ ያም መከራ የሚ​ያ​ገ​ኛ​ቸ​ው​ንና በል​ዑል ዘንድ ሃይ​ማ​ኖ​ትና በጎ ምግ​ባር፥ ጽና​ትም ያላ​ቸ​ውን እርሱ ራሱ ይጠ​ብ​ቃ​ቸ​ዋል።

24 ነገር ግን ከሞ​ቱት ይልቅ በሕ​ይ​ወት የቀ​ሩት ፈጽ​መው ብፁ​ዓን እንደ ሆኑ ዕወቅ።

25 የዚ​ህስ የሕ​ል​ምህ ትር​ጓ​ሜው እን​ደ​ዚህ ነው፤ ከባ​ሕር ሲወጣ ያየ​ኸው ይህ ሰው፥

26 ዓለ​ሙን ሁሉ በእ​ርሱ ያድን ዘንድ ለኋላ ዘመን ልዑል የጠ​በ​ቀው ይህ ነው። እር​ሱም የተ​ረ​ፉ​ትን በሥ​ር​ዐት ያኖ​ራ​ቸ​ዋል።

27 እንደ ጥቅል ነፋስ ከአፉ የእ​ሳት ነበ​ል​ባል፥ የእ​ሳ​ትም ፍሕም ሲወጣ ያየ​ኸው፥

28 ጦሩን ወይም የጦር መሣ​ሪ​ያ​ውን ያላ​ነሣ፥ ግን የከ​በ​ቡ​ት​ንና ሊገ​ድ​ሉት የመ​ጡ​ትን እነ​ዚ​ያን ብዙ​ዎ​ችን ያጠ​ፋ​ቸው ትር​ጓ​ሜው እን​ዲህ ነው።

29 በም​ድር የሚ​ኖ​ሩ​ትን ልዑል የሚ​ያ​ድ​ን​በት ዘመን ይመ​ጣል።

30 ያን​ጊዜ እርስ በእ​ር​ሳ​ቸው ይወ​ነ​ጃ​ጀ​ላሉ።

31 ከተማ ከከ​ተማ ጋር፥ ገጠር ከገ​ጠር ጋር፥ ሕዝብ ከሕ​ዝብ ጋር፥ መን​ግ​ሥ​ታት ከመ​ን​ግ​ሥ​ታት ጋር ይዋ​ጋሉ።

32 ይህም በተ​ደ​ረገ ጊዜ፥ ቀድሞ ያሳ​የ​ሁህ ምል​ክ​ቱም በደ​ረሰ ጊዜ ያን​ጊዜ ከባ​ሕር ሲወጣ ያየ​ኸው ያ ሰው ይገ​ለ​ጣል።

33 “አሕ​ዛ​ብም ሁሉ ቃሉን በሰሙ ጊዜ ሀገ​ሮ​ቻ​ቸ​ውና እርስ በር​ሳ​ቸው የሚ​ጣ​ሉ​በ​ትን ጠባ​ቸ​ውን ይተ​ዋሉ።

34 ቍጥር የሌ​ላ​ቸው ሰዎች እን​ዳ​የ​ሃ​ቸው መጥ​ተው ሊገ​ድ​ሉት ወድ​ደው በአ​ን​ድ​ነት በዝ​ተው ይሰ​በ​ሰ​ባሉ።

35 እርሱ ግን በጽ​ዮን ተራራ ራስ ይቆ​ማል።

36 ያለ ሰው እጅ የተ​ፈ​ጠ​ረው ተራራ ሲወጣ እን​ዳ​የ​ኸው፥ ጽዮን ትመ​ጣ​ለች፤ ተዘ​ጋ​ጅ​ታና ተሠ​ር​ታም ለሁሉ ትታ​ያ​ለች፤

37 እንደ ዓውሎ ነፋስ የሆኑ አሕ​ዛ​ብን በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው የሚ​ዘ​ል​ፋ​ቸው እርሱ ወልድ ነው። የሥ​ራ​ቸ​ው​ንም ክፋት በፊ​ታ​ቸው ይገ​ል​ጥ​ባ​ቸ​ዋል። እንደ እሳት ነበ​ል​ባል የሆ​ኑ​ትም በጽ​ኑዕ የሚ​ሠ​ቃ​ዩ​በ​ትን ይገ​ል​ጣል።

38 እንደ እሳት ፍም የሆ​ኑ​ት​ንም ያለ ድካም ከኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው ጋር ያጠ​ፋ​ቸ​ዋል።

39 “ለእ​ርሱ የሚ​ስ​ማሙ ብዙ​ዎች ወደ እርሱ ሲሰ​በ​ሰቡ ያየ​ኸ​ውም፥

40 እኒህ በአ​ሦር ንጉሥ በስ​ል​ም​ና​ሶር ዘመን ካገ​ራ​ቸው የተ​ማ​ረኩ፥ እር​ሱም በመ​ን​ግ​ሥቱ የማ​ረ​ካ​ቸው፥ በወ​ንዙ ማዶም ያኖ​ራ​ቸው ዘጠኙ ነገ​ድና የነ​ገድ እኩ​ሌታ ናቸው፤ ተመ​ል​ሰ​ውም ሌላ ሆኑ።

41 የወ​ገ​ና​ቸ​ውን ነገድ ይተዉ ዘንድ፥ የሰው ወገን ወደ​ማ​ይ​ኖ​ር​በት ሀገ​ርም ይሄዱ ዘንድ እነ​ርሱ ራሳ​ቸው ይህ​ችን ምክር አወ​ጧት።

42 በሀ​ገ​ራ​ቸው ያል​ጠ​በ​ቁ​ትን ሕግ ይጠ​ብቁ ዘንድ፥

43 መግ​ቢ​ያው ጠባብ ወደ ሆነ ወደ ኤፍ​ራ​ጥ​ስም ገቡ።

44 ያን​ጊ​ዜም ልዑል ተአ​ምር አደ​ረ​ገ​ላ​ቸው፤ የወ​ን​ዙ​ንም ምንጭ እስ​ኪ​ያ​ልፉ ድረስ አቆ​መ​ላ​ቸው።

45 ሀገሩ ግን ዓመት ከመ​ን​ፈቅ ያስ​ሄ​ዳል፤ የሀ​ገ​ሩም ስም አዛፍ ይባ​ላል።

46 “እስከ ኋለ​ኛ​ውም ዘመን ድረስ በዚህ ኖሩ፤ ከዚ​ህም በኋላ ዳግ​መኛ ይመ​ለሱ ዘንድ ባላ​ቸው ጊዜ፦

47 መሻ​ገር ይችሉ ዘንድ የወ​ን​ዙን ምንጭ ልዑል ዳግ​መኛ ያቆ​ም​ላ​ቸ​ዋል።

48 ስለ​ዚ​ህም ስለ አየ​ኸው ነገር ከሕ​ዝቡ አብ​ዛ​ኛ​ዎ​ቹን ይወ​ስ​ዷ​ቸ​ዋል። እነ​ር​ሱም በከ​በ​ረው ቦታዬ ይገ​ኛሉ።

49 በእ​ርሱ ላይ የተ​ሰ​በ​ሰቡ እነ​ዚ​ያን ብዙ​ዎ​ች​ንም ባጠ​ፋ​ቸው ጊዜ ያን​ጊዜ የቀ​ሩ​ትን ሕዝብ ያጸ​ና​ቸ​ዋል።

50 ያን​ጊ​ዜም ብዙ ምል​ክ​ቱን ያሳ​ያ​ቸ​ዋል።”

51 እኔም እን​ዲህ አል​ሁት፥ “አቤቱ ጌታዬ፥ ይህ​ንም ንገ​ረኝ፤ ከባ​ሕር መካ​ከል ሰው ሲወጣ እኔ ያየ​ሁት ስለ ምን​ድን ነው?”

52 እን​ዲ​ህም አለኝ፦ በባ​ሕሩ ጥል​ቀት ውስጥ ያለ​ውን ማንም ማወቅ እን​ደ​ማ​ይ​ችል እን​ደ​ዚ​ሁም በም​ድር ካሉት ወል​ድን ማወቅ የሚ​ችል ማንም የለም፤ ሰዓ​ቱና ቀኑ በደ​ረሰ ጊዜ ነው እንጂ፤ ከእ​ር​ሱም ጋር ያሉት አያ​ው​ቁ​ትም።

53 ያየ​ኸው የሕ​ል​ምህ ትር​ጓ​ሜው ይህ ነው፤ ስለ​ዚ​ህም ለአ​ንተ ብቻ አሳ​የ​ሁህ።

54 ግዳ​ጅ​ህን ትተህ የእ​ኔን ግዳጅ ተከ​ት​ለ​ሃ​ልና ሕጌ​ንም ፈል​ገ​ሃ​ልና።

55 ሕይ​ወ​ት​ህ​ንም ለዕ​ው​ቀት አዘ​ጋ​ጅ​ተ​ሃ​ልና፤ ጥበ​ብ​ንም እናት አድ​ር​ገ​ሃ​ታ​ልና።

56 ስለ​ዚ​ህም ይህን ገለ​ጥ​ሁ​ልህ፤ ዋጋህ በል​ዑል ዘንድ አለና፥ እን​ግ​ዲ​ህስ ወዲህ ከጥ​ቂት ቀን በኋላ ና፤ የም​ነ​ግ​ርህ ሌላ ነገር አለና፥ ድን​ቅ​ንም እተ​ረ​ጕ​ም​ል​ሃ​ለ​ሁና።”

57 በየ​ጊ​ዜው ስለ​ሚ​ያ​ደ​ር​ገው ስለ ድንቅ ሥራ​ውም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ግ​ነ​ውና አከ​ብ​ረው ዘንድ ወደ ምድረ በዳ አልፌ ሄድሁ።

58 ዘመ​ኖ​ቹን ያዘ​ጋ​ጃ​ቸ​ዋ​ልና፥ ይህ​ንም በየ​ዓ​መቱ ያደ​ር​ጋ​ልና። በዚ​ያም ሦስት ቀን ተቀ​መ​ጥሁ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች