La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኤርምያስ 25:4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ባሪ​ያ​ዎ​ቹን ነቢ​ያ​ትን ወደ እና​ንተ ላከ፤ እነ​ር​ሱም ማል​ደው ገሠ​ገሡ፤ እና​ን​ተም አል​ሰ​ማ​ች​ኋ​ቸ​ውም፤ ለመ​ስ​ማ​ትም ጆሮ​አ​ች​ሁን አላ​ዘ​ነ​በ​ላ​ች​ሁም።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

እግዚአብሔር አገልጋዮቹን ነቢያትን ሁሉ ደጋግሞ ወደ እናንተ ላከ፤ ሆኖም አልሰማችሁም፤ ትኵረትም አልሰጣችሁትም።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ጌታም ማልዶ ተነሥቶ ባርያዎቹን ነቢያትን ሁሉ ወደ እናንተ ላከ፤ ልኮም ግን እናንተ አላደመጣችሁም፥ ለመስማትም ጆሮአችሁን አላዘነበላችሁም።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

እግዚአብሔር በተከታታይ አገልጋዮቹን ነቢያቱን ቢልክላችሁም እናንተ ልብ ብላችሁ አላዳመጣችሁም፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

እግዚአብሔርም ማልዶ ተነሥቶ ባሪያዎቹን ነቢያትን ወደ እናንተ ላከ፥ እናንተም አላደመጣችሁም ጆሮአችሁንም አላዘነበላችሁም።

Ver Capítulo



ኤርምያስ 25:4
24 Referencias Cruzadas  

ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ይመ​ል​ሱ​አ​ቸው ዘንድ ነቢ​ያ​ትን ይሰ​ድ​ድ​ላ​ቸው ነበር፤ መሰ​ከ​ሩ​ባ​ቸ​ውም፤ እነ​ርሱ ግን አላ​ደ​መ​ጡም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ምና​ሴ​ንና ሕዝ​ቡን ተና​ገ​ራ​ቸው፤ ግን አል​ሰ​ሙ​ትም።


እና​ን​ተም ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ ይልቅ ክፉ አድ​ር​ጋ​ች​ኋል፤ እነ​ሆም ሁላ​ችሁ እንደ ክፉ ልባ​ችሁ ፍላ​ጎት ሄዳ​ች​ኋል፤ እኔ​ንም አል​ሰ​ማ​ች​ሁም።


እነ​ርሱ ግን አል​ሰ​ሙም፤ ጆሮ​አ​ቸ​ው​ንም አላ​ዘ​ነ​በ​ሉም፤ እን​ዳ​ይ​ሰ​ሙና ተግ​ሣ​ጼን እን​ዳ​ይ​ቀ​በ​ሉም ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ይልቅ አን​ገ​ታ​ቸ​ውን አደ​ነ​ደኑ።”


እነ​ርሱ ግን፥ “እን​ጨ​ክ​ና​ለን፤ ክዳ​ታ​ች​ንን ተከ​ት​ለን እን​ሄ​ዳ​ለን፥ ሁላ​ች​ንም ክፉ ልባ​ች​ንን ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኛ​ትን እና​ደ​ር​ጋ​ለን” አሉ።


የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ቃሌን እን​ዳ​ይ​ሰሙ አን​ገ​ታ​ቸ​ውን አደ​ን​ድ​ነ​ዋ​ልና እነሆ በዚች ከተ​ማና በመ​ን​ደ​ሮ​ችዋ ሁሉ ላይ የተ​ና​ገ​ር​ሁ​ባ​ትን ክፉ ነገር ሁሉ አመ​ጣ​ለሁ።”


በጐ​ሰ​ቈ​ልሽ ጊዜ ተና​ገ​ር​ሁሽ፤ አን​ቺም፦ አል​ሰ​ማም አልሽ፤ ከሕ​ፃ​ን​ነ​ትሽ ጀምሮ ቃሌን አለ​መ​ስ​ማ​ትሽ መን​ገ​ድሽ ነው።


“ከይ​ሁዳ ንጉሥ ከአ​ሞጽ ልጅ ከኢ​ዮ​ስ​ያስ ከዐ​ሥራ ሦስ​ተ​ኛው ዓመት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ባሉት በእ​ነ​ዚህ በሃያ ሦስቱ ዓመ​ታት፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ወደ እኔ መጣ፤ እኔም ማልጄ ተነ​ሥቼ ተና​ገ​ር​ኋ​ችሁ፤ ነገር ግን አል​ሰ​ማ​ች​ሁ​ኝም።”


ለእ​ና​ንተ ጕዳት እን​ዲ​ሆን በእ​ጃ​ችሁ ሥራ ታስ​ቈ​ጡኝ ዘንድ አል​ሰ​ማ​ች​ሁ​ኝም፥” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


የባ​ሪ​ያ​ዎ​ችን የነ​ቢ​ያ​ትን ቃል ትሰሙ ዘንድ በማ​ለዳ ወደ እና​ንተ ብል​ካ​ቸው አል​ሰ​ማ​ች​ሁም።


ይህም የሆ​ነው ቃሌን ስላ​ል​ሰሙ ነው፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ በማ​ለዳ ባሪ​ያ​ዎ​ችን ነቢ​ያ​ትን ወደ እነ​ርሱ ሰድ​ጃ​ለ​ሁና፤ እና​ንተ ግን አል​ሰ​ማ​ች​ሁም፤ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ፊታ​ቸ​ው​ንም ሳይ​ሆን ጀር​ባ​ቸ​ውን ወደ እኔ መለሱ፤ እኔም በማ​ለዳ ተነ​ሥቼ ሳስ​ተ​ም​ራ​ቸው ተግ​ሣ​ጽን ይቀ​በሉ ዘንድ አል​ሰ​ሙም።


ስለ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውም እር​ሱ​ንና ዘሩን አገ​ል​ጋ​ዮ​ቹ​ንም በመ​ዓት እጐ​በ​ኛ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም አል​ሰ​ሙ​ምና የተ​ና​ገ​ር​ሁ​ባ​ቸ​ውን ክፉ ነገር ሁሉ በእ​ነ​ርሱ ላይና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም በሚ​ቀ​መጡ በይ​ሁ​ዳም ሰዎች ላይ አመ​ጣ​ለሁ።”


እኔም፥ “የመ​ለ​ከ​ቱን ድምፅ አድ​ምጡ” ብዬ ጠባ​ቂ​ዎ​ችን ሾም​ሁ​ባ​ቸው፤ እነ​ርሱ ግን፥ “አና​ዳ​ም​ጥም” አሉ።


የቀደሙት ነቢያት ለአባቶቻችሁ እንዲህ ብለው ሰብከዋል፦ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ከክፉ መንገዳችሁና ከክፉ ሥራችሁ ተመለሱ፣ እነርሱ ግን አልሰሙም፥ እኔንም አላደመጡም፣ እንደ እነርሱ አትሁኑ፥ ይላል እግዚአብሔር።


ለሚ​ና​ገ​ረው እንቢ እን​ዳ​ትሉ ተጠ​ን​ቀቁ፤ እነ​ርሱ በደ​ብረ ሲና የተ​ገ​ለ​ጠ​ላ​ቸ​ውን እንቢ ስለ አሉት ካል​ዳኑ፥ ከሰ​ማይ ከመ​ጣው ፊታ​ች​ንን ብን​መ​ልስ እኛማ እን​ዴታ?