Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ኤርምያስ 18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የሸ​ክ​ላ​ውና የሸ​ክላ ሠሪው ምሳሌ

1 ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ወደ ኤር​ም​ያስ የመጣ ቃል፥ እን​ዲ​ህም አለው፦

2 “ተነ​ሥ​ተህ ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ውረድ፤ በዚ​ያም ቃሌን አሰ​ማ​ሃ​ለሁ።”

3 ወደ ሸክላ ሠሪ​ውም ቤት ወረ​ድሁ፤ እነ​ሆም ሥራ​ውን በዓ​ለት ላይ ሲሠራ አገ​ኘ​ሁት።

4 ከጭ​ቃም ይሠ​ራው የነ​በ​ረው ዕቃ ከሸ​ክላ ሠሪው እጅ ወደቀ፤ ሸክላ ሠሪ​ውም እንደ ወደደ ዳግ​መኛ ሌላ ዕቃ አድ​ርጎ ሠራው።

5 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል ወደ እኔ እን​ዲህ ሲል መጣ።

6 “የእ​ስ​ራ​ኤል ቤት ሆይ! ይህ ሸክላ ሠሪ እን​ደ​ሚ​ሠራ በውኑ እኔ በእ​ና​ንተ ዘንድ መሥ​ራት አይ​ቻ​ለ​ኝ​ምን? እነሆ ጭቃው በሸ​ክላ ሠሪ እጅ እን​ዳለ፥ እን​ዲሁ እና​ንተ በእኔ እጅ አላ​ችሁ።

7 አጠ​ፋ​ቸ​ውና እደ​መ​ስ​ሳ​ቸው ዘንድ በሕ​ዝብ ላይና በመ​ን​ግ​ሥት ላይ ቍርጥ ነገ​ርን ተና​ገ​ርሁ፤

8 ስለ እነ​ርሱ የተ​ና​ገ​ር​ሁ​ባ​ቸው ሕዝብ ከክ​ፋ​ታ​ቸው ቢመ​ለሱ፥ እኔ አደ​ር​ግ​ባ​ቸው ዘንድ ካሰ​ብ​ሁት ክፉ ነገር እጸ​ጸ​ታ​ለሁ።

9 በሕ​ዝ​ብም በመ​ን​ግ​ሥ​ታ​ትም ላይ እሠ​ራ​ቸ​ውና እተ​ክ​ላ​ቸው ዘንድ ቍርጥ ነገ​ርን እና​ገ​ራ​ለሁ፤

10 በፊቴ ክፉን ነገር ቢያ​ደ​ርጉ ቃሌ​ንም ባይ​ሰሙ፥ እኔ አደ​ር​ግ​ላ​ቸው ዘንድ ስለ ተና​ገ​ር​ሁት መል​ካም ነገር እጸ​ጸ​ታ​ለሁ።”

11 አሁን እን​ግ​ዲህ ለይ​ሁዳ ሰዎ​ችና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ለሚ​ኖሩ፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “እነሆ ክፉ ነገር እፈ​ጥ​ር​ባ​ች​ኋ​ለሁ፤ ምክ​ር​ንም እመ​ክ​ር​ባ​ች​ኋ​ለሁ፤ አሁ​ንም ሁላ​ችሁ ከክፉ መን​ገ​ዳ​ችሁ ተመ​ለሱ፤ መን​ገ​ዳ​ች​ሁ​ንና ሥራ​ች​ሁ​ንም አቅኑ ብለህ ተና​ገ​ራ​ቸው።”

12 እነ​ርሱ ግን፥ “እን​ጨ​ክ​ና​ለን፤ ክዳ​ታ​ች​ንን ተከ​ት​ለን እን​ሄ​ዳ​ለን፥ ሁላ​ች​ንም ክፉ ልባ​ች​ንን ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኛ​ትን እና​ደ​ር​ጋ​ለን” አሉ።

13 ስለ​ዚህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “የእ​ስ​ራ​ኤል ድን​ግል ያደ​ረ​ገ​ች​ውን በጣም የሚ​ያ​ስ​ደ​ነ​ግ​ጠ​ውን ነገር የሚ​ሰ​ሙት እን​ዳለ አሕ​ዛ​ብን ጠይቁ።”

14 ምንጭ ከዓ​ለት ይጠ​ፋ​ልን? በረ​ዶስ ከሊ​ባ​ኖስ ይጠ​ፋ​ልን? ወራጅ ውኃስ በኀ​ይ​ለኛ ነፋስ ይመ​ለ​ሳ​ልን?

15 ሕዝቤ ግን ረስ​ተ​ው​ኛል፤ ለከ​ንቱ ነገ​ርም አጥ​ነ​ዋል፤ የቀ​ድ​ሞ​ውን ጐዳና ትተው ወደ ጠማ​ማ​ውና ወደ ሰን​ከ​ል​ካ​ላው መን​ገድ ለመ​ሄድ በመ​ን​ገ​ዳ​ቸው ተሰ​ና​ከሉ።

16 ምድ​ራ​ቸ​ውን ለጥ​ፋ​ትና ለዘ​ለ​ዓ​ለም ማፍ​ዋጫ አድ​ር​ገ​ዋል፤ የሚ​ያ​ል​ፍ​ባት ሁሉ ይደ​ነ​ቃል፤ ራሱ​ንም ያነ​ቃ​ን​ቃል።

17 በጠ​ላት ፊት እንደ በረሃ ዐውሎ ነፋስ እበ​ት​ና​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በጥ​ፋ​ታ​ቸ​ውም ቀን ጀር​ባ​ዬን እንጂ ፊቴን አላ​ሳ​ያ​ቸ​ውም።


በኤ​ር​ም​ያስ ላይ የተ​ደ​ረገ ሴራ

18 እነ​ር​ሱም፥ “ሕግ ከካ​ህን፥ ምክ​ርም ከጠ​ቢብ፥ ቃልም ከነ​ቢይ አይ​ጠ​ፋ​ምና ኑ፤ በኤ​ር​ም​ያስ ላይ ምክ​ርን እን​ም​ከር። ኑ፤ በም​ላስ እን​ም​ታው፤ ቃሉ​ንም ሁሉ አና​ዳ​ምጥ” አሉ።

19 “አቤቱ! አድ​ም​ጠኝ፤ የክ​ር​ክ​ሬ​ንም ቃል ስማ።

20 ለሰ​ው​ነቴ ጕድ​ጓ​ድን ቈፍ​ረ​ዋል፤ በውኑ በመ​ል​ካም ፈንታ ክፉ ይመ​ለ​ሳ​ልን? ስለ እነ​ርሱ በመ​ል​ካም እና​ገር ዘንድ፥ ቍጣ​ህ​ንም ከእ​ነ​ርሱ ትመ​ልስ ዘንድ በፊ​ትህ እንደ ቆምሁ አስብ።

21 ስለ​ዚህ ልጆ​ቻ​ቸ​ውን ለራብ ስጥ፤ ለሰ​ይ​ፍም እጅ አሳ​ል​ፈህ ስጣ​ቸው፤ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም የወ​ላድ መካ​ንና መበ​ለ​ቶች ይሁኑ፤ ወን​ዶ​ቻ​ቸ​ውም በሞት ይጥፉ፤ ጐል​ማ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም በጦ​ር​ነት ጊዜ በሰ​ይፍ ይመቱ።

22 ሊይ​ዙኝ ጕድ​ጓድ ቈፍ​ረ​ዋ​ልና፥ ለእ​ግ​ሮ​ችም ወጥ​መድ ሸሽ​ገ​ዋ​ልና፥ በቤ​ታ​ቸው ጩኸት ይሰማ፤ ድን​ገ​ትም በላ​ያ​ቸው ወን​በ​ዴን አም​ጣ​ባ​ቸው።

23 አንተ ግን አቤቱ! ይገ​ድ​ሉኝ ዘንድ በላዬ የመ​ከ​ሩ​ትን ምክር ሁሉ ታው​ቃ​ለህ፤ በደ​ላ​ቸ​ው​ንም ይቅር አት​በል፤ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንም ከፊ​ትህ አት​ደ​ም​ስስ፤ በፊ​ት​ህም ይው​ደቁ፤ በቍ​ጣህ ጊዜ እን​ዲሁ አድ​ር​ግ​ባ​ቸው።”

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos