La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘፀአት 32:5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

አሮ​ንም በአ​የው ጊዜ መሠ​ዊ​ያ​ውን በፊቱ ሠራ፤ አሮ​ንም፥ “ነገ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓል ነው” ሲል አወጀ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

አሮን ይህን ባየ ጊዜ በወርቅ ጥጃው ፊት ለፊት መሠዊያ ሠርቶ፣ “ነገ ለእግዚአብሔር በዓል ይሆናል” ብሎ ዐወጀ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

አሮንም አየውና መሠዊያን በፊቱ ሠራ፤ አሮንም፦ “ነገ የጌታ በዓል ነው” ሲል አወጀ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

አሮንም ይህን ባየ ጊዜ በወርቁ ጥጃ ፊት መሠዊያ ሠርቶ “ነገ ለእግዚአብሔር ክብር በዓል ይደረጋል” ሲል አስታወቀ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

አሮንም ባየው ጊዜ መሠዊያን በፊቱ ሠራ፤ አሮንም፦ ነገ የእግዚአብሔር በዓል ነው ሲል አወጀ።

Ver Capítulo



ዘፀአት 32:5
18 Referencias Cruzadas  

ለወ​ልደ አዴር መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችም፥ “ለጌ​ታ​ችሁ፦ ለእኔ አገ​ል​ጋ​ይህ በመ​ጀ​መ​ሪያ የላ​ክ​ህ​ብ​ኝን ሁሉ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ ይህን ነገር ግን አደ​ር​ገው ዘንድ አይ​ቻ​ለ​ኝም” በሉት አላ​ቸው። መል​ክ​እ​ክ​ተ​ኞ​ችም ተመ​ል​ሰው ይህን ነገር ነገ​ሩት።


ኢዩም፥ “ለበ​ዓል መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ች​ሁን አንጹ” አላ​ቸው፤ እነ​ር​ሱም አዋጅ ነገሩ።


ካህ​ኑም ኦርያ ንጉሡ አካዝ ከደ​ማ​ስቆ እንደ ላከ​ለት መሠ​ዊ​ያ​ውን ሁሉ ሠራ፤ እን​ዲ​ሁም ካህኑ ኦርያ ንጉሡ አካዝ ከደ​ማ​ስቆ እስ​ኪ​መጣ ድረስ ሠራው።


እንደ ተጻ​ፈም ብዙ​ዎቹ አላ​ደ​ረ​ጉ​ትም ነበ​ርና የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፋሲካ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያደ​ርጉ ዘንድ እን​ዲ​መጡ ከቤ​ር​ሳ​ቤህ ጀምሮ እስከ ዳን ድረስ ለእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ አዋጅ እን​ዲ​ነ​ገር ወሰኑ።


ሙሴም አለው፥ “እኛ ከታ​ና​ና​ሾ​ቻ​ች​ንና ከሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎ​ቻ​ችን፥ ከወ​ን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ቻ​ችን ጋር እን​ሄ​ዳ​ለን፤ በጎ​ቻ​ች​ን​ንና ላሞ​ቻ​ች​ን​ንም እን​ወ​ስ​ዳ​ለን። የአ​ም​ላ​ካ​ችን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓል ነውና።”


ይህም ቀን መታ​ሰ​ቢያ ይሁ​ና​ችሁ፤ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዓል ታደ​ር​ጉ​ታ​ላ​ችሁ፤ ለልጅ ልጃ​ች​ሁም ሥር​ዐት ሆኖ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ታደ​ር​ጉ​ታ​ላ​ችሁ።


ሙሴም መሠ​ዊያ ሠራ፤ ስሙ​ንም “ምም​ሕ​ፃን” ብሎ ጠራው፤


ከእ​ጃ​ቸ​ውም ተቀ​ብሎ በመ​ቅ​ረጫ ቀረ​ጸው፤ ቀልጦ የተ​ሠራ ጥጃም አደ​ረ​ገው፤ እር​ሱም፥ “እስ​ራ​ኤል ሆይ፥ እነ​ዚህ ከግ​ብፅ ምድር ያወ​ጡህ አማ​ል​ክ​ትህ ናቸው” አላ​ቸው።


አሮ​ንም በነ​ጋው ማልዶ ተነሣ፤ የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም ሠዋ፤ የደ​ኅ​ን​ነት መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም አቀ​ረበ ሕዝ​ቡም ሊበ​ሉና ሊጠጡ ተቀ​መጡ፤ ሊዘ​ፍ​ኑም ተነሡ።


ኤፍ​ሬም መሠ​ዊ​ያን አብ​ዝ​ቶ​አ​ልና የወ​ደ​ደው መሠ​ዊያ ለኀ​ጢ​አት ሆነ​በት።


እስ​ራ​ኤል ፈጣ​ሪ​ውን ረስ​ቶ​አል፤ መስ​ገ​ጃ​ዎ​ች​ንም ሠር​ቶ​አል፤ ይሁ​ዳም የተ​መ​ሸ​ጉ​ትን ከተ​ሞች አብ​ዝ​ቶ​አል፤ እኔ ግን በከ​ተ​ሞች ላይ እሳ​ትን እሰ​ድ​ዳ​ለሁ፤ መሠ​ረ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ትበ​ላ​ለች።


“ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እን​ዲህ ብለህ ንገ​ራ​ቸው፦ ቅዱ​ሳት ጉባ​ኤ​ያት ብላ​ችሁ የም​ት​ጠ​ሩ​አ​ቸው በዓ​ላቴ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓ​ላት እነ​ዚህ ናቸው።


ያች​ንም ቀን ቅድ​ስት ጉባኤ ብላ​ችሁ ታው​ጃ​ላ​ችሁ፤ የተ​ግ​ባር ሥራ ሁሉ አታ​ድ​ር​ጉ​ባት፤ በም​ት​ቀ​መ​ጡ​በት ሀገር ሁሉ ለልጅ ልጃ​ችሁ የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ነው።


“የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት፥ የእ​ህ​ሉ​ንም ቍር​ባን፥ መሥ​ዋ​ዕ​ቱ​ንም፥ የመ​ጠ​ጡ​ንም ቍር​ባን፥ በየ​ቀኑ የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታቀ​ር​ቡ​ባ​ቸው ዘንድ የተ​ቀ​ደሱ በዓ​ላት እን​ዲ​ሆኑ የም​ታ​ው​ጁ​አ​ቸው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓ​ላት እነ​ዚህ ናቸው።


እነ​ዚህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓ​ላት፥ በየ​ዘ​መ​ና​ቸው የም​ታ​ው​ጁ​አ​ቸው፥ የተ​ቀ​ደሱ ጉባ​ኤ​ያት ናቸው።


አሁ​ንም በዓ​ላ​ች​ሁን አድ​ርጉ፤ ነገር ግን እው​ነ​ትና ንጽ​ሕና ባለው እርሾ ነው እንጂ በአ​ሮ​ጌው እርሾ፥ በኀ​ጢ​አ​ትና በክ​ፋት እር​ሾም አይ​ደ​ለም።


ሳኦ​ልም በዚያ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊ​ያን ሠራ፤ ይኸ​ውም ሳኦል ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሠ​ራው የመ​ጀ​መ​ሪያ መሠ​ዊያ ነው።