La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኢሳይያስ 37:19 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

አማ​ል​ክ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም በእ​ሳት አቃ​ጥ​ለ​ዋል፤ የእ​ን​ጨ​ትና የድ​ን​ጋይ የሰው እጅ ሥራም ነበሩ እንጂ አማ​ል​ክት አል​ነ​በ​ሩ​ምና ስለ​ዚህ አጥ​ፍ​ተ​ዋ​ቸ​ዋል።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

አማልክታቸውን ወደ እሳት ጥለዋል፤ በሰው እጅ የተቀረጹ የድንጋይና የዕንጨት ምስሎች እንጂ አማልክት አልነበሩምና።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

አማልክቶቻቸውንም በእሳት ላይ ጥለዋል፤ የእንጨትና የድንጋይ፥ የሰው እጅ ሥራ ነበሩ እንጂ አማልክት አልነበሩምና ስለዚህ አጥፍተዋቸዋል።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

እንጨቱን በመጥረብ፥ ድንጋዩን በማለዘብ በሰው እጅ የተሠሩ ከንቱ የሆኑ አማልክታቸውን በእሳት አቃጥለው አጥፍተዋል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

አማልክቶቻቸውንም በእሳት ላይ ጥለዋል፥ የእንጨትና የድንጋይ የሰው እጅ ሥራ ነበሩ እንጂ አማልክት አልነበሩምና ስለዚህ አጥፍተዋቸዋል።

Ver Capítulo



ኢሳይያስ 37:19
25 Referencias Cruzadas  

ጣዖ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም በዚያ ተዉ፤ ዳዊ​ትና ሰዎ​ቹም ወሰ​ዱ​አ​ቸው።


የሠ​ሩ​ት​ንም ጥጃ ወስዶ በእ​ሳት አቀ​ለ​ጠው፤ ፈጨው፤ አደ​ቀ​ቀ​ውም፤ በው​ኃም ላይ በተ​ነው፤ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች አጠ​ጣ​ቸው።


እርሱ በልቡ እን​ዲህ አይ​መ​ስ​ለ​ውም፤ እን​ዲ​ህም አያ​ስ​ብም፤ ነገር ግን ማጥ​ፋት፥ ጥቂት ያይ​ደ​ሉ​ት​ንም አሕ​ዛብ መቍ​ረጥ በልቡ አለ።


በጣ​ዖ​ታ​ቸ​ውና ጣቶ​ቻ​ቸው በሠ​ሩ​አ​ቸው የእ​ጃ​ቸው ሥራ​ዎች አይ​ተ​ማ​መ​ኑም፤ ለር​ኵ​ሰ​ታ​ቸ​ውም ዛፎ​ችን አይ​ቈ​ር​ጡም።


ምድ​ራ​ቸ​ውም በእ​ጆ​ቻ​ቸው በሠ​ሩ​አ​ቸው ጣዖ​ታት ተሞ​ል​ታ​ለች፤ በጣ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ለሠ​ሩ​አ​ቸው ይሰ​ግ​ዳሉ።


ነገር ግን ሙታን ሕይ​ወ​ትን አያ​ዩ​አ​ትም፤ ባለ መድ​ኀ​ኒ​ቶ​ችም አያ​ስ​ነ​ሡም፤ ስለ​ዚ​ህም አንተ አም​ጥ​ተ​ሃ​ቸ​ዋል፤ አጥ​ፍ​ተ​ሃ​ቸ​ው​ማል፤ ወን​ዶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ሁሉ አስ​ወ​ግ​ደ​ሃል።


እና​ንተ ከየት ናችሁ? ከየ​ትስ ሠሯ​ችሁ? ከም​ድር የሚ​መ​ር​ጧ​ች​ሁም የረ​ከሱ አይ​ደ​ሉ​ምን?


የሚ​ሠ​ሩ​አ​ቸ​ውም በከ​ንቱ ይሠ​ሩ​አ​ቸ​ዋል።


አና​ጢ​ውም አን​ጥ​ረ​ኛ​ውን፥ በመ​ዶ​ሻም የሚ​ያ​ሳ​ሳ​ውን መስፍ መች​ውን አጽ​ናና፤ ስለ ማጣ​በቅ ሥራ​ውም፥ “መል​ካም ነው” አለ፤ እን​ዳ​ይ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ስም በች​ን​ካር አጋ​ጠ​መው።


የቀ​ረ​ው​ንም እን​ጨት ጣዖት አድ​ርጎ ምስል ይቀ​ር​ጽ​በ​ታል፤ በፊ​ቱም ተጐ​ን​ብሶ ይሰ​ግ​ዳል፤ ወደ እር​ሱም እየ​ጸ​ለየ፥ “አም​ላኬ ነህና አድ​ነኝ” ይላል።


ስለ ክፋ​ታ​ቸ​ውም ሁሉ፥ እኔን ስለ ተዉ፥ ለሌ​ሎ​ችም አማ​ል​ክት ስለ ሠዉ፥ ለእ​ጃ​ቸ​ውም ሥራ ስለ ሰገዱ፥ ፍር​ዴን በእ​ነ​ርሱ ላይ እና​ገ​ራ​ለሁ።


እና​ን​ተም፦ ሰማ​ይ​ንና ምድ​ርን ያል​ፈ​ጠሩ እነ​ዚህ አማ​ል​ክት ከም​ድር ላይ፥ ከሰ​ማ​ይም በታች ፈጽ​መው ይጥፉ ትሉ​አ​ቸ​ዋ​ላ​ችሁ።


በውኑ ሰው አማ​ል​ክት ያል​ሆ​ኑ​ትን ለራሱ አማ​ል​ክ​ትን አድ​ርጎ ይሠ​ራ​ልን?


አሕ​ዛብ አማ​ል​ክት ያል​ሆኑ አማ​ል​ክ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ይለ​ውጡ አንደ ሆነ እዩ፤ ነገር ግን ሕዝቤ ክብ​ራ​ቸ​ውን ለማ​ይ​ረባ ነገር ለወጡ።


ይህ ደግሞ በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ ነው፤ ሠራ​ተኛ ሠራው፤ እር​ሱም አም​ላክ አይ​ደ​ለም፤ ሰማ​ርያ ሆይ! እን​ቦ​ሳሽ ተቅ​በ​ዝ​ብ​ዞ​አ​ልና።


ነገር ግን ቀድሞ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ባለ​ማ​ወ​ቃ​ችሁ፥ በባ​ሕ​ር​ያ​ቸው አማ​ል​ክት ላል​ሆኑ ተገ​ዝ​ታ​ችሁ ነበር።