Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ከዚ​ህም በኋላ ፈጣሪ ለዚያ ንስር ይህን ቃል በነ​ገ​ረው ጊዜ፥

2 የቀ​ረው ያ ራስ ጠፋ፤ወደ እርሱ የመጡ እነ​ዚ​ያም ክን​ፎች ተነሡ፤ እነ​ር​ሱም ይገዙ ዘንድ ተነሡ፤ በጥ​ፍ​ራ​ቸ​ውም ይታ​ወኩ ነበር።

3 ከዚህ በኋላ እነ​ር​ሱም ጠፉ፤ ሥጋ​ቸ​ውም ሁሉ ተቃ​ጠለ፤ ምድ​ርም ፈጽማ ደነ​ገ​ጠች። እኔም ከብዙ ምር​ምር የተ​ነሣ ደነ​ገ​ጥሁ፤ በጽኑ ፍር​ሀ​ትም ነቃሁ።

4 ልቡ​ና​ዬ​ንም እን​ዲህ አል​ኋት፥ “የል​ዑ​ልን ሥራ ስት​መ​ረ​ምሪ አንቺ ይህን ሁሉ አደ​ረ​ግ​ሽኝ።

5 ሰው​ነ​ቴም ደከ​መች፤ ልቡ​ና​ዬም እጅግ ተጨ​ነ​ቀች፤ በብዙ ፍር​ሀት ተይዤ ምንም ኀይል የለ​ኝም፤ በዚ​ችም ሌሊት ደነ​ገ​ጥሁ።

6 አሁ​ንም ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ያጸ​ናኝ ዘንድ ወደ ልዑል እጸ​ል​ያ​ለሁ።”

7 እን​ዲ​ህም አልሁ፥ “አቤቱ ጌታዬ በዐ​ይ​ኖ​ችህ ፊት ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን ካገ​ኘሁ፥ በአ​ን​ተም ዘንድ ራሴን ብፁዕ ካሰ​ኘሁ፥ ጸሎ​ቴም በፊ​ትህ ከደ​ረ​ሰች፥

8 አድ​ነኝ፤ አጽ​ና​ኝም፤ ነፍ​ሴም ፈጽማ ደስ ይላት ዘንድ የሚ​ያ​ስ​ፈራ የዚ​ህን ሕልም ትር​ጓሜ ለባ​ሪ​ያህ ንገ​ረው።

9 በኋላ ዘመን የሚ​ደ​ረ​ገ​ው​ንና የዓ​ለ​ሙን ኅል​ፈት ያሳ​የ​ኸኝ አንተ ብፁዕ አድ​ር​ገ​ኸ​ኛ​ልና።”


የራ​እዩ ትር​ጓሜ

10 መል​አ​ኩም እን​ዲህ አለኝ፥ “ያየ​ኸው የዚህ ሕል​ምህ ትር​ጓሜ እን​ዲህ ነው።

11 ከባ​ሕር ሲወጣ ያየ​ኸው ይህ ንስር ለወ​ን​ድ​ምህ ለዳ​ን​ኤል በሕ​ልም የታ​የ​ችው አራ​ተ​ኛዋ መን​ግ​ሥት ናት።

12 ነገር ግን ዛሬ ለአ​ንተ እኔ እን​ደ​ተ​ረ​ጐ​ም​ሁ​ልህ ለእ​ርሱ አል​ተ​ረ​ጐ​ም​ሁ​ለ​ትም።

13 እነሆ፥ ዘመን ይመ​ጣል፤ በም​ድ​ርም ከእ​ር​ስዋ አስ​ቀ​ድሞ ከነ​በ​ሩት መን​ግ​ሥ​ታት ይልቅ የም​ታ​ስ​ፈራ መን​ግ​ሥት ትነ​ሣ​ለች።

14 በእ​ር​ሷም ዐሥራ ሁለት ነገ​ሥ​ታት በተ​ከ​ታ​ታይ ይነ​ግ​ሣሉ።

15 ቀጥሎ የሚ​ነ​ግ​ሠ​ውም በዘ​መኑ ከዐ​ሥራ ሁለቱ ነገ​ሥ​ታት ፈጽሞ የሚ​ጸና ነው።

16 ያየ​ሃ​ቸው የእ​ኒህ የዐ​ሥራ ሁለቱ ክን​ፎች ትር​ጓሜ ይህ ነው።

17 ቃልን ሲና​ገር ያየ​ኸው ይህም ከሥ​ጋው መካ​ከል ነው እንጂ ከራሱ የሚ​ወጣ ሁለ​ተ​ኛው አይ​ደ​ለም።

18 ትር​ጓ​ሜ​ውም እን​ዲህ ነው፤ ከዚያ መን​ግ​ሥት ወገን መካ​ከል ብዙ ሁከት ይፈ​ጠ​ራል፤ መን​ግ​ሥ​ትም ለመ​ው​ደቅ ትን​ገ​ዳ​ገ​ዳ​ለች፤ ነገር ግን ጸንታ ትኖ​ራ​ለች እንጂ ያን​ጊዜ አት​ወ​ድ​ቅም።

19 ከክ​ን​ፎ​ቹም ራሶች ሲወጡ ያየ​ኸው ይህ፥

20 ትር​ጓ​ሜው እን​ደ​ዚህ ነው፤ ስም​ንቱ ነገ​ሥ​ታት በእ​ር​ስዋ ይነ​ግ​ሣሉ፤ ዘመ​ና​ቸ​ውም የከፋ፥ ወራ​ታ​ቸ​ውም ያጠረ ይሆ​ናል፤ ከእ​ነ​ርሱ ሁለቱ ግን በዘ​መ​ና​ቸው መካ​ከል ፈጥ​ነው ይጠ​ፋሉ።

21 ነገር ግን አራቱ መን​ግ​ሥ​ታት የሚ​ጠ​ፉ​በት ጊዜ እስ​ኪ​ደ​ርስ ድረስ ይጠ​በ​ቃሉ፤ ሁለ​ቱም ለብዙ ዘመን ይጠ​በ​ቃሉ።

22 “ዝም ብለው ያየ​ሃ​ቸው እነ​ዚህ ሦስቱ ራሶ​ችም፦

23 ትር​ጓ​ሜው እን​ዲህ ነው፤ ልዑል በኋላ ዘመን ሦስት ነገ​ሥ​ታ​ትን ያስ​ነ​ሣል፤ በው​ስ​ጧም ብዙ​ውን ያድ​ሳሉ፤ ምድ​ር​ንም ያሠ​ቃ​ዩ​አ​ታል።

24 በው​ስጧ የሚ​ኖ​ሩ​ት​ንም ከእ​ነ​ርሱ በፊት ከነ​በ​ሩት ሁሉ ይልቅ እጅግ ያሠ​ቃ​ዩ​አ​ቸ​ዋል። ስለ​ዚ​ህም የን​ስሩ ራሶች ተባሉ።

25 እነ​ርሱ የመ​ን​ግ​ሥት መጀ​መ​ሪ​ያ​ዎች፥ የመ​ን​ግ​ሥ​ትም መጨ​ረ​ሻ​ዎች ናቸ​ውና።

26 ይህም ሲጠፋ ያየ​ኸው አንዱ ታላቅ ራስ በታ​ላቅ ጻእር ተጨ​ንቆ በመ​ኝ​ታው የሚ​ሞት ከእ​ነ​ርሱ አንዱ ነው።

27 የቀ​ሩት እነ​ዚያ ሁለቱ ግን በጦር ይሞ​ታሉ።

28 አንዱ ኋለ​ኛ​ውም በጦር ይሞ​ታል።

29 “በቀኝ በኩል ወደ አለው ራሱ የሄ​ዱት እነ​ዚያ ያየ​ሃ​ቸው ሁለት ራሶ​ችም፥

30 ትር​ጓ​ሜው ይህ ነው፤ ልዑል በኋላ ዘመን የጠ​በ​ቃ​ቸው፥ መጀ​መ​ሪ​ያው ጥፋት የሚ​ደ​ረ​ግ​ባ​ቸው ናቸው፤ አንተ እን​ዳ​የ​ኸ​ውም ብዙ ጸብ ይደ​ረ​ጋል።

31 ከዱር እያ​ገሣ ሲወጣ ያንም ንስር በሰ​ማ​ኸው ሁሉ ነገር ሲና​ገ​ረ​ውና በኀ​ጢ​አቱ ሁሉ ሲዘ​ል​ፈው ያየ​ኸው ይህ አን​በ​ሳም፥

32 ልዑል ለኋላ ዘመን የጠ​በ​ቀው፥ ከዳ​ዊ​ትም ወገን የሚ​ወ​ለ​ደው ነው፤ መጥ​ቶም ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ይነ​ግ​ራ​ቸ​ዋል፤ ስለ​በ​ደ​ላ​ቸ​ውም ይዘ​ል​ፋ​ቸ​ዋል፤ በፊ​ታ​ቸ​ውም ፍዳ​ቸ​ውን ይገ​ል​ጥ​ባ​ቸ​ዋል።

33 በሕ​ይ​ወት ሳሉም አስ​ቀ​ድሞ በፍ​ርድ ያቆ​ማ​ቸ​ዋል፤ ከዘ​ለ​ፋ​ቸ​ውም በኋላ ያን​ጊዜ ያጠ​ፋ​ቸ​ዋል።

34 ትሩ​ፋ​ኑን ግን በቸ​ር​ነቱ በከ​በረ አው​ራጃ ይቤ​ዣ​ቸ​ዋል፤ አስ​ቀ​ድ​ሜም የነ​ገ​ር​ሁህ የፍ​ርድ ቀን እስ​ኪ​ደ​ርስ ድረስ ደስ ያሰ​ኛ​ቸ​ዋል።

35 ያየ​ኸው ሕል​ምህ ይህ ነው፤ ትር​ጓ​ሜ​ውም እን​ደ​ዚህ ነው።

36 ልዑል ይህን ምሥ​ጢር አንተ ብቻ እን​ድ​ታ​ው​ቀው አደ​ረ​ገ​ልህ።

37 ነገር ግን ይህን ያየ​ኸ​ውን ሁሉ ጻፈው፤ በተ​ሰ​ወረ ቦታም አኑ​ረው።

38 ይህ​ንም ምሥ​ጢር በል​ቡ​ና​ቸው ለመ​ጠ​በቅ እን​ዲ​ቻ​ላ​ቸው አንተ ለም​ታ​ው​ቃ​ቸው ለጠ​ቢ​ባን አስ​ተ​ም​ራ​ቸው።

39 አንተ ግን ልዑል ሊያ​ሳ​ይህ የሚ​ወ​ድ​ደ​ውን ታይ ዘንድ ዳግ​መኛ ሰባት ቀን በዚህ ተቀ​መጥ።”


ሕዝቡ ወደ ዕዝራ እንደ ተሰ​በ​ሰቡ

40 ከዚ​ህም በኋላ ከእኔ ተለ​ይቶ ሄደ፤ እኒያ ሰባት ቀኖች እን​ዳ​ለፉ፥ እኔም ወደ ከተማ እን​ዳ​ል​ገ​ባሁ ሰዎች ሁሉ በሰሙ ጊዜ፥ ሕዝቡ ሁሉ ትን​ሹም ትል​ቁም ተሰ​ብ​ስ​በው ወደ እኔ መጡ፤ እን​ዲ​ህም አሉኝ፦

41 “እኛን ትተ​ኸን በዚህ ምድረ በዳ ትኖር ዘንድ ምን በደ​ል​ንህ? ምንስ ግፍ ሠራ​ን​ብህ?

42 ከሚ​ለ​ቅ​ሙት ፍሬ ሁሉ እንደ አንድ ፍሬ፥ በጨ​ለማ ቦታ ውስ​ጥም እንደ አለ መብ​ራት፥ ከጥ​ል​ቅም እን​ደ​ሚ​ያ​ድን የመ​ር​ከብ ወደብ ከነ​ቢ​ያት ሁሉ አንድ አንተ ብቻ ቀር​ተ​ህ​ል​ና​ልና።

43 ወይስ ያገ​ኘ​ችን መከራ አል​በ​ቃ​ች​ን​ምን?

44 አን​ተስ የም​ት​ለ​የን ከሆነ ጽዮን በተ​ቃ​ጠ​ለች ጊዜ ብን​ኖር በተ​ሻ​ለን ነበር፤

45 በዚያ ከሞ​ቱት ሰዎች እኛ የም​ን​ሻል አይ​ደ​ለ​ን​ምና።” በታ​ላቅ ድም​ፅም አለ​ቀሱ።

46 እኔም መለ​ስ​ሁ​ላ​ቸው፤ እን​ዲ​ህም አል​ሁ​አ​ቸው፥ “የያ​ዕ​ቆብ ልጆች እመኑ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ወገ​ኖች አት​ዘኑ።

47 መታ​ሰ​ቢ​ያ​ችን በል​ዑል ፊት አለና፥ የማ​ይ​ዘ​ነ​ጋን እር​ሱም ጽኑዕ ነውና።

48 እኔስ አል​ተ​ዋ​ች​ሁም፤ ከእ​ና​ን​ተም አል​ር​ቅም፤ ነገር ግን ወደ​ዚህ ቦታ የመ​ጣ​ሁት ስለ ጽዮን ጥፋት እለ​ምን ዘንድ ነው፤ በደ​ስ​ታ​ችን ላይ ስለ መጣ​ብ​ንም መከራ ይቅ​ር​ታን እለ​ምን ዘንድ ነው።

49 አሁ​ንም ሁላ​ችሁ ወደ​የ​ቤ​ታ​ችሁ ግቡ፤ እኔም ወደ እና​ንተ እመ​ጣ​ለሁ።”

50 ከእ​ነ​ዚ​ያም ወራ​ቶች በኋላ ሕዝቡ እን​ዳ​ዘ​ዝ​ኋ​ቸው ወደ ከተማ ወደ​የ​ቤ​ታ​ቸው ገቡ።

51 እኔ ግን መል​አኩ እን​ዳ​ዘ​ዘኝ በዚያ ቦታ በም​ድረ በዳው ውስጥ ሰባት ቀን ተቀ​መ​ጥሁ፤ ከም​ድረ በዳ ፍሬ ብቻም ተመ​ገ​ብሁ፤ በእ​ነ​ዚ​ያም በሰ​ባቱ ቀኖች ከም​ድረ በዳው ቅጠል በላሁ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች