La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ነህምያ 11:22 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ሥራ ላይ ከነ​በሩ መዘ​ም​ራን ከአ​ሳፍ ልጆች ወገን የሚካ ልጅ፥ የመ​ታ​ንያ ልጅ፥ የሐ​ሳ​ብያ ልጅ፥ የባኒ ልጅ ኦዚ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሌ​ዋ​ው​ያን አለቃ ነበረ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

በኢየሩሳሌም የሌዋውያኑ ዋና አለቃ የሚካ ልጅ፣ የመታንያ ልጅ፣ የሐሸብያ ልጅ፣ የባኒ ልጅ ኦዚ ነበረ፤ ኦዚ በእግዚአብሔር ቤት አገልግሎት ለሚዘመረው መዝሙር ኀላፊ ከነበሩት ከአሳፍ ዘሮች አንዱ ነበረ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

በእግዚአብሔር ቤት ሥራ ላይ ከነበሩ መዘምራን ከአሳፍ ልጆች ወገን የሚካ ልጅ፥ የማታንያ ልጅ፥ የሓሻብያ ልጅ፥ የባኒ ልጅ ዑዚ በኢየሩሳሌም የሌዋውያን አለቃ ነበረ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

በኢየሩሳሌም የሌዋውያን አለቃ ዑዚ የባሂ ልጅ፥ የሖሻብያ ልጅ፥ የማታንያ ልጅ፥ የሚካ ልጅ ነበር። ዑዚ የቤተ መቅደስ መዘምራን ኀላፊ የነበረው የአሳፍ ዘር ነበር።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

በእግዚአብሔርም ቤት ሥራ ላይ ከነበሩ መዘምራን ከአሳፍ ልጆች ወገን የሚካ ልጅ የመታንያ ልጅ የሐሸብያ ልጅ የባኒ ልጅ አዚ በኢየሩሳሌም የሌዋውያን አለቃ ነበረ።

Ver Capítulo



ነህምያ 11:22
19 Referencias Cruzadas  

ለሜ​ም​ፌ​ቡ​ስ​ቴም ሚካ የተ​ባለ ታናሽ ልጅ ነበ​ረው፤ በሲ​ባም ቤት ያሉ ሁሉ ለሜ​ም​ፌ​ቡ​ስቴ ያገ​ለ​ግሉ ነበር።


ደግ​ሞም አሴ​ብ​ያ​ስን፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ከሜ​ራሪ ልጆች ወገን የነ​በ​ረ​ውን ኢሳ​ይ​ያ​ስን፥ ሃያ​ውን ወን​ድ​ሞ​ቹ​ንና ልጆ​ቻ​ቸ​ውን።


ሚካ፥ ሬሆብ፥ ሐሳ​ብያ፤


ሆድያ፥ ባኒ፥ ባኑን።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት አለቃ የአ​ኪ​ጦብ ልጅ፥ የማ​ር​ዮት ልጅ፥ የሳ​ዶቅ ልጅ፥ የሜ​ሱ​ላም ልጅ፥ የኬ​ል​ቅ​ያስ ልጅ ሣርያ፥


ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም መቶ ሃያ ስም​ንት ጽኑ​ዓን ኀያ​ላን፤ አለ​ቃ​ቸ​ውም የሐ​ጊ​ዶ​ሌም ልጅ ዘብ​ዲ​ሔል ነበረ።


አለ​ቃ​ቸ​ውም የዝ​ክሪ ልጅ ኢዮ​ኤል ነበረ፤ የሰ​ኑ​ዋም ልጅ ይሁዳ በከ​ተ​ማው ላይ ሁለ​ተኛ ነበረ።


መለ​ከ​ትም ይዘው ከካ​ህ​ናቱ ልጆች አያ​ሌ​ዎች፥ የአ​ሳ​ፍም ልጅ የዘ​ኩር ልጅ የሚ​ካያ ልጅ የመ​ታ​ንያ ልጅ የሰ​ማ​ዕያ ልጅ የዮ​ና​ታን ልጅ ዘካ​ር​ያስ፤


መዕ​ሤያ፥ ሰማ​ዕያ፥ ኤል​የ​ዜር፥ ኦዚ፥ ዮሐ​ናን፥ ሚል​ክያ፥ ኤላም፥ ኤዝር፥ መዘ​ም​ራ​ኑም በታ​ላቅ ድምፅ ዘመሩ፤ አለ​ቃ​ቸ​ውም ይዝ​ረ​አያ ነበረ።


በዳ​ዊ​ትም ዘመን አሳፍ የመ​ዘ​ም​ራን አለቃ ነበር፤ እነ​ር​ሱም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በዜማ ያመ​ሰ​ግኑ ነበር።


በዕቃ ቤቶ​ችም ላይ ካህ​ኑን ሰሌ​ም​ያን፥ ጸሓ​ፊ​ው​ንም ሳዶ​ቅን፥ ከሌ​ዋ​ው​ያ​ኑም ፈዳ​ያን ሾምሁ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር የመ​ታ​ንያ ልጅ የዘ​ኩር ልጅ ሐናን ነበረ፤ እነ​ር​ሱም የታ​መኑ ሆነው ተገኙ፤ ሥራ​ቸ​ውም ለወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ማከ​ፋ​ፈል ነበረ።


ከእ​ር​ሱም በኋላ ሌዋ​ው​ያ​ንና የባኒ ልጅ ሬሁም ሠሩ። በአ​ጠ​ገ​ባ​ቸ​ውም የቅ​ዒላ ግዛት እኩ​ሌ​ታና የአ​ው​ራ​ጃ​ዎ​ችዋ ገዢ አሰ​ብያ ሠራ።


ደግሞ ኢያ​ሱና ባኒ፥ ሰራ​ብያ፥ ያሚን፥ ዓቁብ፥ ሳባ​ታይ፥ ሆዲያ፥ መዕ​ሤያ፥ ቆሊጣ፥ ዓዛ​ርያ፥ ኢዮ​ዛ​ባድ፥ ሐናን፥ ፌል​ዕያ፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑም ሕጉን ለሕ​ዝቡ ያስ​ተ​ምሩ ነበር፤ ሕዝ​ቡም በየ​ስ​ፍ​ራ​ቸው ቆመው ነበር።


አሁ​ንም በገዛ ደሙ የዋ​ጃ​ትን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤተ ክር​ስ​ቲ​ያን ትጠ​ብቁ ዘንድ መን​ፈስ ቅዱስ እና​ን​ተን ጳጳ​ሳት አድ​ርጎ ለሾ​መ​ባት ለመ​ን​ጋው ሁሉና ለራ​ሳ​ችሁ ተጠ​ን​ቀቁ።