La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘሌዋውያን 24:9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ለአ​ሮ​ንና ለል​ጆ​ቹም ይሁን፤ በእ​ሳት ከተ​ደ​ረ​ገው ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍር​ባን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ለእ​ርሱ ቅዱሰ ቅዱ​ሳን ነውና በተ​ቀ​ደሰ ስፍራ ይብ​ሉት።”

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ኅብስቱ የአሮንና የልጆቹ ድርሻ ነው፤ በተቀደሰ ስፍራም ይበሉታል፤ ለእግዚአብሔር በእሳት ከሚቀርበው መሥዋዕት እጅግ የተቀደሰ ድርሻቸው ነውና።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እርሱም ለአሮንና ለልጆቹ ይሆናል፤ ለጌታም በእሳት ከሚቀርበው ቁርባን ውስጥ በዘለዓለም ሥርዓት፥ ለእርሱ እጅግ ቅዱስ የሆነ ድርሻ ነውና በተቀደሰ ስፍራ ይብሉት።”

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ይህም የእስራኤል ሕዝብ ዘወትር ሊፈጽሙት የሚገባ የቃል ኪዳን ሥርዓት ነው። ኅብስቱ የአሮንና የልጅ ልጆቹ ድርሻ ይሆናል፤ እነርሱም በተቀደሰ ቦታ ይብሉት፤ እርሱ ለእግዚአብሔር የሚቃጠል ቅዱስ መሥዋዕት ሆኖ ከቀረበ በኋላ ለካህናቱ የተለየ ቋሚ ድርሻ ይሆናል።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ለአሮንና ለልጆቹም ይሁን፤ በእሳት ከተደረገው ከእግዚአብሔር ቍርባን በዘላለም ሥርዓት ለእርሱ ቅዱሰ ቅዱሳን ነውና በተቀደሰ ስፍራ ይብሉት።

Ver Capítulo



ዘሌዋውያን 24:9
17 Referencias Cruzadas  

በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ውስጥ በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት ካለው መጋ​ረጃ ውጭ አሮ​ንና ልጆቹ ከማታ እስከ ማለዳ ድረስ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ያብ​ሩት፤ በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ዘንድ ለልጅ ልጃ​ቸው የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ይሁን።


ሙሴም አሮ​ንን፥ የተ​ረ​ፉ​ለ​ትን ልጆ​ቹን አል​ዓ​ዛ​ር​ንና ኢታ​ም​ርን አላ​ቸው፥ “ቅዱሰ ቅዱ​ሳን ነውና ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከሆ​ነው ከእ​ሳት ቍር​ባን የቀ​ረ​ውን የስ​ን​ዴ​ውን ቍር​ባን ውሰዱ፤ ቂጣም አድ​ር​ጋ​ችሁ በመ​ሠ​ዊ​ያው አጠ​ገብ ብሉት፤


“ቅዱሰ ቅዱ​ሳን ነውና፥ የሕ​ዝ​ቡ​ንም ኀጢ​አት እን​ድ​ት​ሸ​ከሙ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት እን​ድ​ታ​ስ​ተ​ሰ​ር​ዩ​ላ​ቸው ይህን ትበሉ ዘንድ ለእ​ና​ንተ ሰጥ​ቶ​ታ​ልና ስለ ምን የኀ​ጢ​አ​ትን መሥ​ዋ​ዕት በቅ​ዱሱ ስፍራ አል​በ​ላ​ች​ሁም?


የቅ​ዱ​ሱ​ንና የቅ​ዱሰ ቅዱ​ሳ​ኑን የአ​ም​ላ​ኩን መባ ይብላ፤


አባቱ ግብ​ፃዊ የነ​በረ የእ​ስ​ራ​ኤ​ላ​ዊት ሴት ልጅ በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች መካ​ከል ወጣ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ላ​ዊቱ ሴት ልጅና አንድ እስ​ራ​ኤ​ላዊ ሰው በሰ​ፈር ውስጥ ተጣሉ፤


ስብና ደም እን​ዳ​ት​በሉ በም​ት​ኖ​ሩ​በት ሁሉ ለልጅ ልጃ​ችሁ የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ነው።”


ልብ​ሱ​ንም ያወ​ል​ቃል፤ ሌላም ልብስ ይለ​ብ​ሳል፤ አመ​ዱ​ንም ተሸ​ክሞ ከሰ​ፈሩ ንጹሕ ወደ ሆነ ስፍራ ወደ ውጭ ያወ​ጣ​ዋል።


ከእ​ር​ሱም የተ​ረ​ፈ​ውን አሮ​ንና ልጆቹ ይበ​ሉ​ታል፤ ቂጣ ሆኖ በተ​ቀ​ደ​ሰው ስፍራ ይበ​ላል፤ በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ዙሪያ ባለው አደ​ባ​ባይ ይበ​ሉ​ታል።


“አሮ​ን​ንና ልጆ​ቹን እን​ዲህ ብለህ እዘ​ዛ​ቸው፦ የሚ​ቃ​ጠ​ለው የመ​ሥ​ዋ​ዕቱ ሕግ ይህ ነው፤ የመ​ሠ​ዊ​ያው እሳት በላዩ እየ​ነ​ደ​ደች እስ​ኪ​ነጋ ትተ​ዉ​ታ​ላ​ችሁ።


ማኅ​በ​ሩ​ንም ሁሉ ወደ ምስ​ክሩ ድን​ኳን ደጃፍ ሰብ​ስ​ባ​ቸው።”


ሙሴም አሮ​ን​ንና ልጆ​ቹን አላ​ቸው፥ “ሥጋ​ውን በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ደጃፍ በተ​ቀ​ደ​ሰው ቦታ ቀቅሉ፤ አሮ​ንና ልጆቹ ይብ​ሉት ብሎ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ዘ​ዘኝ በዚያ እር​ሱ​ንና በቅ​ድ​ስ​ናው መሶብ ያለ​ውን እን​ጀራ ብሉ።


እናንተ ግን፦ የእግዚአብሔር ገበታ ርኩስ ነው፣ ፍሬውና መብሉም የተናቀ ነው በማለታችሁ አስነቀፋችሁት።


አብያተር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ፥ ከካህናት በቀር መብላት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደ ሰጣቸው ከቶ አላነበባችሁምን?” አላቸው።


ወደ ቤተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ገባ፥ ከካ​ህ​ና​ቱም ብቻ በቀር ሊበ​ሉት የማ​ይ​ገ​ባ​ውን የመ​ሥ​ዋ​ዕ​ቱን ኅብ​ስት ወስዶ እንደ በላ፥ አብ​ረ​ውት ለነ​በ​ሩ​ትም እንደ ሰጣ​ቸው አላ​ነ​በ​ባ​ች​ሁ​ምን?


ካህኑ አቤ​ሜ​ሌ​ክም በእ​ርሱ ፋንታ ትኩስ እን​ጀራ ይደ​ረግ ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ከአ​ለው ኅብ​ስት በቀር ሌላ እን​ጀራ አል​ነ​በ​ረ​ምና የቍ​ር​ባ​ኑን ኅብ​ስት ሰጠው።