La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኤርምያስ 39:6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የባ​ቢ​ሎ​ንም ንጉሥ የሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስን ልጆች በዐ​ይኑ ፊት በዴ​ብ​ላታ ገደ​ላ​ቸው፤ የባ​ቢ​ሎ​ንም ንጉሥ የይ​ሁ​ዳን ታላ​ላ​ቆች ሁሉ ገደለ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

በሪብላም የባቢሎንም ንጉሥ የሴዴቅያስን ወንዶች ልጆች፣ አባታቸው እያየ ገደላቸው፤ የይሁዳንም ባለሥልጣኖች ሁሉ ገደላቸው፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

የባቢሎንም ንጉሥ የሴዴቅያስን ልጆች ዓይኑ እያየ በሪብላ ገደላቸው፤ የባቢሎንም ንጉሥ የይሁዳን መሳፍንት ሁሉ ገደለ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ይኸውም በሪብላ ንጉሥ ሴዴቅያስ ዐይኑ እያየ ልጆቹ እንዲገደሉ ተደረገ፤ የይሁዳ ባለሥልጣኖችም ሁሉ ሞት ተፈረደባቸው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

የባቢሎንም ንጉሥ የሴዴቅያስን ልጆች በዓይኑ ፊት በሪብላ ገደላቸው፥ የባቢሎንም ንጉሥ የይሁዳን ከበርቴዎች ሁሉ ገደለ።

Ver Capítulo



ኤርምያስ 39:6
19 Referencias Cruzadas  

ልጄ ሲሞት አላ​የ​ውም ብላ ቀስት ተወ​ር​ውሮ የሚ​ደ​ር​ስ​በ​ትን ያህል ርቃ በአ​ን​ጻሩ እየ​ተ​መ​ለ​ከ​ተች፥ ፊት ለፊት ተቀ​መ​ጠች፤ ቃል​ዋ​ንም አሰ​ምታ አለ​ቀ​ሰች።


አለ​ዚ​ያም ብላ​ቴ​ናው ከእኛ ጋር ከሌለ እኔ ወደ አባ​ታ​ችን እን​ዴት እሄ​ዳ​ለሁ? አባ​ታ​ች​ንን የሚ​ያ​ገ​ኘ​ውን መከራ እን​ዳ​ላይ።”


ነገሩ እን​ደ​ዚህ አይ​ደ​ለም፤ ወደ አባ​ቶ​ችህ እሰ​በ​ስ​ብ​ሃ​ለሁ፥ በሰ​ላ​ምም ወደ መቃ​ብ​ርህ ትሰ​በ​ሰ​ባ​ለህ፤ በዚ​ህም ስፍ​ራና በሚ​ኖ​ሩ​በት ላይ የማ​መ​ጣ​ውን ክፉ ነገር ዐይ​ኖ​ችህ አያ​ዩም።” ይህ​ንም ለን​ጉሡ ነገ​ሩት።


የሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስ​ንም ልጆች በፊቱ ገደ​ሉ​አ​ቸው፤ የሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስ​ንም ዐይ​ኖች አወጡ፤ በሰ​ን​ሰ​ለ​ትም አሰ​ሩት፤ ወደ ባቢ​ሎ​ንም ወሰ​ዱት።


እነሆ፥ ወደ አባ​ቶ​ችህ እሰ​በ​ስ​ብ​ሃ​ለሁ፤ በሰ​ላ​ምም ወደ መቃ​ብ​ርህ ትሰ​በ​ሰ​ባ​ለህ፤ በዚ​ህም ስፍ​ራና በሚ​ኖ​ሩ​በት ላይ የማ​መ​ጣ​ውን ክፉ ነገር ሁሉ ዐይ​ኖ​ችህ አያ​ዩም” ያለ​ቻ​ቸ​ው​ንም ነገር ለን​ጉሡ አስ​ረ​ዱት።


ሕፃ​ኖ​ቻ​ቸ​ው​ንም በፊ​ታ​ቸው ይጨ​ፈ​ጭ​ፋሉ፤ ቤቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ይበ​ዘ​ብ​ዛሉ፤ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ያስ​ነ​ው​ራሉ።


አለ​ቆ​ችዋ ያል​ቃሉ፤ ነገ​ሥ​ታ​ቷና መሳ​ፍ​ንቷ ይጠ​ፋሉ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላ​ልና፦ እነሆ አን​ተን ከወ​ዳ​ጆ​ችህ ሁሉ ጋር አፈ​ል​ስ​ሃ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸው ሰይፍ ይወ​ድ​ቃሉ፤ ዐይ​ኖ​ች​ህም ያያሉ፤ አን​ተ​ንና ይሁ​ዳ​ንም ሁሉ በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ እጅ አሳ​ልፌ እሰ​ጣ​ለሁ፤ እር​ሱም ወደ ባቢ​ሎን ያፈ​ል​ሳ​ቸ​ዋል፤ በሰ​ይ​ፍም ይገ​ድ​ላ​ቸ​ዋል።


ከዚህ በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የይ​ሁ​ዳን ንጉሥ ሴዴ​ቅ​ያ​ስ​ንና አገ​ል​ጋ​ዮ​ቹን፥ ከቸ​ነ​ፈ​ርና ከሰ​ይፍ፥ ከራ​ብም በዚ​ህች ከተማ የቀ​ሩ​ትን ሕዝ​ቡ​ንም በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር እጅ፥ በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ነፍ​ሳ​ቸ​ው​ንም በሚ​ሹት እጅ አሳ​ልፌ እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እር​ሱም በሰ​ይፍ ስለት ይመ​ታ​ቸ​ዋል፤ አያ​ዝ​ን​ላ​ቸ​ውም፤ አይ​ራ​ራ​ላ​ቸ​ውም፤ አይ​ም​ራ​ቸ​ውም።”


አን​ተም በር​ግጥ ትያ​ዛ​ለህ፤ በእ​ጁም አል​ፈህ ትሰ​ጣ​ለህ እንጂ ከእጁ አታ​መ​ል​ጥም፤ ዐይ​ን​ህም የባ​ቢ​ሎ​ንን ንጉሥ ዐይን ታያ​ለች፤ እር​ሱም ከአ​ንተ ጋር አፍ ለአፍ ይና​ገ​ራል፤ ወደ ባቢ​ሎ​ንም ትገ​ባ​ለህ።


ሚስ​ቶ​ች​ህ​ንና ልጆ​ች​ህ​ንም ሁሉ ወደ ከለ​ዳ​ው​ያን ያወ​ጣሉ፤ አን​ተም በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ እጅ ትያ​ዛ​ለህ እንጂ ከእ​ጃ​ቸው አታ​መ​ል​ጥም፤ ይህ​ችም ከተማ በእ​ሳት ትቃ​ጠ​ላ​ለች።”


የባ​ቢ​ሎ​ንም ንጉሥ የሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስን ልጆች በፊቱ ገደ​ላ​ቸው፤ የይ​ሁ​ዳ​ንም አለ​ቆች ሁሉ ደግሞ በዴ​ብ​ላታ ገደ​ላ​ቸው።


ስማ​ቸ​ውን ያስ​ጠሩ ሰዎች ሁሉ በመ​ን​ኰ​ራ​ኵ​ርና በሠ​ረ​ገላ፥ በአ​ሕ​ዛ​ብም ጉባኤ ይመ​ጡ​ብ​ሻል፤ ጋሻና አላ​ባሽ ጋሻ፥ ራስ ቍርም ይዘው በዙ​ሪ​ያሽ ጥበቃ ያደ​ር​ጋሉ፤ ፍር​ድ​ንም እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እንደ ፍር​ዳ​ቸ​ውም ይፈ​ር​ዱ​ብ​ሻል።


ከመ​ን​ጋው የተ​መ​ረ​ጠ​ውን ውሰድ፤ አጥ​ን​ቶ​ቹም እን​ዲ​በ​ስሉ በበ​ታ​ችዋ እሳት አን​ድድ፤ አፍ​ላው፤ በእ​ጅጉ ይፍላ፤ አጥ​ን​ቶ​ቹም በው​ስ​ጥዋ ይቀ​ቀሉ።


በእግዚአብሔርም መሥዋዕት ቀን አለቆችንና የንጉሥን ልጆች እንግዳ ልብስ የሚለብሱትንም ሁሉ እቀጣለሁ።


ዐይ​ኖ​ች​ህም ከሚ​ያ​ዩት የተ​ነሣ ዕብድ ትሆ​ና​ለህ።