አቤቱ፥ ሰው ረግጦኛልና ይቅር በለኝ፤ ሁልጊዜም ሰልፍ አስጨንቆኛል።
እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማ፤ ልመናዬን ቸል አትበል፤
ለመዘምራን አለቃ፥ በበገናዎች፥ የዳዊት ትምህርት።
አምላክ ሆይ! ጸሎቴን ስማ፤ ልመናዬንም ቸል አትበል!
እጅህን ከአርያም ላክ፥ ከብዙ ውኃም አድነኝ፤ ከባዕድ ልጆችም እጅ፥
አቤቱ፥ በኀይሌ እወድድሃለሁ።
ሕዝብህን አድን፥ ርስትህንም ባርክ፥ ጠብቃቸው፥ ለዘለዓለሙም ከፍ ከፍ አድርጋቸው።
የአማልክት ልጆች ሆይ፥ ለእግዚአብሔር አምጡ፥ የጊደሮችን ጥጃ ለእግዚአብሔር አምጡ። ክብርንና ምስጋናን ለእግዚአብሔር አምጡ፥
አቤቱ፥ ቃሌን አድምጥ፥ ጩኸቴንም አስተውል፤
አቤቱ፥ በቍጣህ አትቅሠፈኝ፥ በመቅሠፍትህም አትገሥጸኝ።
ነፍሴ ለእግዚአብሔር የምትገዛ አይደለችምን? መድኀኒቴ ከእርሱ ዘንድ ናትና።
አቤቱ፥ በጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል፥ ለአንተም በኢየሩሳሌም ጸሎት ይቀርባል።
በረዳታችን በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፥ ለያዕቆብም አምላክ እልል በሉ።
ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና፥ የያዕቆብም አምላክ ፍርድ ነውና።
እግዚአብሔር አምላኬ የሚናገረኝን አደምጣለሁ፤ ሰላምን ለሕዝቡና ለጻድቃኑ፥ ልባቸውንም ወደ እርሱ ለሚመልሱ ይናገራልና።
እግዚአብሔር ለሕዝቡ፥ በውስጥዋም ለተወለዱት አለቆችዋ በመጽሐፍ ይነግራቸዋል።
አንተ ድምፄን ሰማህ፤ ጆሮህንም ከልመናዬ አትመልስ።
በጠራሁና በጮኽሁ ጊዜ ጸሎቴ ተከለከለ።
የጌታ ዐይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፤ ጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል፤ የጌታ ፊት ግን ክፉ ነገርን በሚያደርጉ ላይ ነው።”