Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 61 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ ስለ ኤዶ​ታም የዳ​ዊት መዝ​ሙር።

1 ነፍሴ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የም​ት​ገዛ አይ​ደ​ለ​ች​ምን? መድ​ኀ​ኒቴ ከእ​ርሱ ዘንድ ናትና።

2 እርሱ አም​ላኬ መድ​ኀ​ኒ​ቴም ነውና፤ እርሱ ረዳቴ ነው ሁል​ጊ​ዜም አል​ታ​ወ​ክም።

3 እስከ መቼ በሰው ላይ ትቆ​ማ​ላ​ችሁ? እና​ንተ ሁላ​ችሁ እን​ዳ​ዘ​ነ​በለ ግድ​ግዳ እንደ ፈረ​ሰም ቅጥር ትገ​ድ​ሉ​ታ​ላ​ችሁ።

4 ነገር ግን ክብ​ሬን ይሽሩ ዘንድ መከሩ፥ በጥ​ሜም ሮጥሁ፤ በአ​ፋ​ቸው ይባ​ር​ካሉ፥ በል​ባ​ቸ​ውም ይረ​ግ​ማሉ።

5 ነገር ግን ነፍሴ፥ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትገ​ዛ​ለች፥ ተስ​ፋዬ ከእ​ርሱ ዘንድ ናትና።

6 እርሱ አም​ላኬ መድ​ኃ​ኒ​ቴም ነውና፤ እርሱ ረዳቴ ነውና፥ አል​ታ​ወ​ክም።

7 መድ​ኃ​ኒቴ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፤ ክብ​ሬም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፥ የረ​ድ​ኤቴ አም​ላክ፥ ተስ​ፋ​ዬም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው።

8 የአ​ሕ​ዛብ ማኅ​በር ሁላ​ችሁ፥ በእ​ርሱ ታመኑ፥ ልባ​ች​ሁ​ንም በፊቱ አፍ​ስሱ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ረዳ​ታ​ችን ነው።

9 ነገር ግን የሰው ልጆች ሁሉ ከንቱ ናቸው፥ የሰው ልጆ​ችም ሐሰ​ተ​ኞች ናቸው፤ በሚ​ዛ​ንም ይበ​ድ​ላሉ፥ እነ​ር​ሱስ በፍ​ጹም ከንቱ ናቸው።

10 ዐመ​ፃን ተስፋ አታ​ድ​ርጉ፥ ቅሚ​ያ​ንም አት​ተ​ማ​መ​ኑት፤ ባለ​ጠ​ግ​ነት ቢበዛ ልባ​ች​ሁን አታ​ኩሩ።

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አንድ ጊዜ ተና​ገረ፥ እኔም ይህን ብቻ ሰማሁ፤ ይቅ​ርታ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነውና፥

12 አቤቱ፥ ኀይ​ልም ያንተ ነው፤ አንተ ለእ​ያ​ን​ዳ​ንዱ እንደ ሥራው ትከ​ፍ​ለ​ዋ​ለ​ህና።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos