Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 17 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ ከሳ​ኦል እጅና ከጠ​ላ​ቶቹ ሁሉ እጅ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባዳ​ነው ቀን በዚህ መዝ​ሙር ቃል ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ና​ገ​ረው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባሪያ የዳ​ዊት መዝ​ሙር።

1 አቤቱ፥ በኀ​ይሌ እወ​ድ​ድ​ሃ​ለሁ።

2 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀይሌ፥ አም​ባዬ፥ መድ​ኀ​ኒቴ፥ አም​ላኬ፥ በእ​ር​ሱም የም​ተ​ማ​መ​ን​በት ረዳቴ፥ መታ​መ​ኛ​ዬና የደ​ኅ​ን​ነቴ ቀንድ፥ መጠ​ጊ​ያ​ዬም ነው።

3 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በጠ​ራ​ሁት ጊዜ ከጠ​ላ​ቶቼ እድ​ና​ለሁ።

4 የሞት ጣር ያዘኝ፥ የዐ​መፅ ፈሳ​ሽም አወ​ከኝ፤

5 የሲ​ኦል ጣር ከበ​በኝ፤ የሞት ወጥ​መ​ድም ደረ​ሰ​ብኝ።

6 በጨ​ነ​ቀኝ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ጠራ​ሁት፥ ወደ አም​ላ​ኬም ጮኽሁ፤ በቤተ መቅ​ደ​ሱም ቃሌን ሰማኝ፥ ጩኸ​ቴም በፊቱ ወደ ጆሮው ገባ።

7 ምድ​ርም ተን​ቀ​ጠ​ቀ​ጠች፥ ተና​ወ​ጠ​ችም፥ የተ​ራ​ሮ​ችም መሠ​ረ​ቶች ተነ​ቃ​ነቁ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተቈ​ጥ​ቶ​አ​ልና ተን​ቀ​ጠ​ቀጡ።

8 ከቍ​ጣው ጢስ ወጣ፥ ከፊ​ቱም እሳት ነደደ፤ ፍምም ከእ​ርሱ በራ።

9 ሰማ​ዮ​ችን ዝቅ ዝቅ አደ​ረገ፥ ወረ​ደም፥ ጭጋግ ከእ​ግሩ በታች ነበረ።

10 በኪ​ሩ​ቤ​ልም ላይ ተቀ​ምጦ በረረ፥ በነ​ፋ​ስም ክንፍ በረረ።

11 መሰ​ወ​ሪ​ያ​ውን ጨለማ አደ​ረገ፤ በዙ​ሪ​ያ​ውም ድን​ኳኑ፤ ውኃ​ዎች በደ​መ​ና​ዎች ውስጥ ጠቈሩ።

12 በፊቱ ካለው ብር​ሃን የተ​ነሣ ደመ​ና​ትና በረዶ የእ​ሳት ፍምም በፊቱ አለፉ።

13 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በሰ​ማ​ያት አን​ጐ​ደ​ጐደ፥ ልዑ​ልም ቃሉን ሰጠ።

14 ፍላ​ጻ​ውን ላከ፥ በተ​ና​ቸ​ውም፤ መብ​ረ​ቆ​ችን አበዛ አወ​ካ​ቸ​ውም።

15 አቤቱ፥ ከተ​ግ​ሣ​ጽህ፥ ከመ​ዓ​ት​ህም መን​ፈስ እስ​ት​ን​ፋስ የተ​ነሣ፥ የው​ኆች ምን​ጮች ታዩ፥ የዓ​ለም መሠ​ረ​ቶ​ችም ተገ​ለጡ።

16 ከአ​ር​ያም ላከ፥ ወሰ​ደ​ኝም፥ ከብዙ ውኆ​ችም አወ​ጣኝ።

17 ከብ​ር​ቱ​ዎች ጠላ​ቶቼ ከሚ​ጠ​ሉ​ኝም አዳ​ነኝ፥ በር​ት​ተ​ው​ብኝ ነበ​ርና።

18 በመ​ከ​ራዬ ቀን ደረ​ሱ​ብኝ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን መጠ​ጊ​ያዬ ሆነ።

19 ወደ ሰፊ ሥፍ​ራም አወ​ጣኝ፤ ወድ​ዶ​ኛ​ልና አዳ​ነኝ።

20 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ጽድቄ ይሰ​ጠ​ኛል፤ እንደ እጆቼ ንጽ​ሕ​ናም ይከ​ፍ​ለ​ኛል።

21 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መን​ገድ ጠብ​ቄ​አ​ለ​ሁና፥ አም​ላ​ኬ​ንም አል​በ​ደ​ል​ሁም።

22 ፍርዱ ሁሉ ሁል​ጊዜ በፊቴ ነበ​ረና፥ ጽድ​ቁም ከእኔ አል​ራ​ቀም።

23 ከእ​ርሱ ጋር ንጹሕ እሆ​ና​ለሁ። ከኀ​ጢ​አ​ቴም እጠ​በ​ቃ​ለሁ።

24 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እንደ ጽድቄ ይሰ​ጠ​ኛል። እንደ እጆ​ቼም ንጽ​ሕና በዐ​ይ​ኖቹ ፊት ይከ​ፍ​ለ​ኛል።

25 ከጻ​ድቅ ሰው ጋር ጻድቅ ትሆ​ና​ለህ፤ ከቅን ሰው ጋርም ቅን ትሆ​ና​ለህ፤

26 ከን​ጹ​ሕም ሰው ጋር ንጹሕ ትሆ​ና​ለህ፤ ከጠ​ማ​ማም ጋር ጠማማ ትሆ​ና​ለህ፥

27 አንተ የተ​ዋ​ረ​ደ​ውን ሕዝብ ታድ​ና​ለ​ህና፥ የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞ​ችን ዐይ​ኖች ግን ታዋ​ር​ዳ​ለህ።

28 አቤቱ አንተ መብ​ራ​ቴን ታበ​ራ​ለ​ህና፤ አም​ላኬ ጨለ​ማ​ዬን ያበ​ራል።

29 በአ​ንተ ከጥ​ፋት እድ​ና​ለ​ሁና፥ በአ​ም​ላ​ኬም ቅጥ​ሩን እዘ​ል​ላ​ለሁ።

30 የአ​ም​ላኬ መን​ገዱ ንጹሕ ነው፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል የነ​ጠረ ነው፥ በእ​ርሱ ለሚ​ታ​መ​ኑት ሁሉ መታ​መ​ኛ​ቸው ነው።

31 ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቀር አም​ላክ ማን ነው? ከአ​ም​ላ​ካ​ች​ንስ በቀር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማን ነው?

32 ኀይ​ልን የሚ​ያ​ስ​ታ​ጥ​ቀኝ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፥ መን​ገ​ዴ​ንም ንጹሕ የሚ​ያ​ደ​ር​ጋት፥

33 እግ​ሮ​ቼን እንደ ዋልያ እግ​ሮች የሚ​ያ​ረታ በከ​ፍ​ታም ቦታ የሚ​ያ​ቆ​መኝ፥

34 እጆ​ቼን ሰልፍ የሚ​ያ​ስ​ተ​ምር፤ ለክ​ን​ዴም የናስ ቀስት አደ​ረገ።

35 ለደ​ኅ​ን​ነ​ቴም መታ​መ​ኛን ሰጠኝ። ቀኝ​ህም ተቀ​በ​ለኝ፥ ትም​ህ​ር​ት​ህም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ያጠ​ና​ኛል። የሚ​ያ​ስ​ተ​ም​ረ​ኝም ተግ​ሣ​ጽህ ነው።

36 አረ​ማ​መ​ዴን በበ​ታቼ አሰ​ፋህ፥ ሰኰ​ና​ዬም አል​ደ​ከ​መም።

37 ጠላ​ቶ​ቼን አሳ​ድ​ዳ​ቸ​ዋ​ለሁ፥ እይ​ዛ​ቸ​ዋ​ለ​ሁም፥ እስ​ካ​ጠ​ፋ​ቸ​ውም ድረስ አል​መ​ለ​ስም።

38 አስ​ጨ​ን​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ መቆ​ምም አይ​ች​ሉም፥ ከእ​ግ​ሬም በታች ይወ​ድ​ቃሉ።

39 በሰ​ል​ፍም ኀይ​ልን ታስ​ታ​ጥ​ቀ​ኛ​ለህ፤ በበ​ላዬ የቆ​ሙ​ትን ሁሉ በበ​ታቼ ትጥ​ላ​ቸ​ዋ​ለህ።

40 የጠ​ላ​ቶቼን ጀርባ ሰጠ​ኸኝ፥ የሚ​ጠ​ሉ​ኝ​ንም አጠ​ፋ​ሃ​ቸው።

41 ጮኹ፥ የሚ​ረ​ዳ​ቸ​ውም አጡ። ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ጮኹ፥ አል​ሰ​ማ​ቸ​ውም።

42 በነ​ፋስ ፊት እን​ዳለ ትቢያ እፈ​ጫ​ቸ​ዋ​ለሁ፥ እንደ አደ​ባ​ባ​ይም ጭቃ እረ​ግ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ።

43 ከሕ​ዝብ ክር​ክር አድ​ነኝ፥ የአ​ሕ​ዛ​ብም ራስ አድ​ር​ገህ ትሾ​መ​ኛ​ለህ፥ የማ​ላ​ው​ቀው ሕዝ​ብም ይገ​ዛ​ል​ኛል።

44 በጆሮ ሰም​ተው ተገ​ዙ​ልኝ፤ የባ​ዕድ ልጆች ዋሹኝ።

45 የባ​ዕድ ልጆች አረጁ፥ በመ​ገ​ን​ዳ​ቸ​ውም ተሰ​ና​ከሉ።

46 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕያው ነው፥ አም​ላ​ኬም ቡሩክ ነው፥ የመ​ድ​ኀ​ኒ​ቴም አም​ላክ ከፍ ከፍ አለ።

47 አም​ላኬ በቀ​ሌን ይመ​ል​ስ​ል​ኛል። አሕ​ዛ​ብን በበ​ታቼ ያስ​ገ​ዛ​ል​ኛል።

48 ከጥ​ፉ​ዎች ጠላ​ቶቼ የሚ​ታ​ደ​ገኝ እርሱ ነው፤ በእኔ ላይ ከቆ​ሙ​ትም ከፍ ከፍ የሚ​ያ​ደ​ር​ገኝ እርሱ ነው፥ ከግ​ፈኛ ሰው አድ​ነኝ።

49 አቤቱ፥ ስለ​ዚህ በአ​ሕ​ዛብ ዘንድ አመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ለሁ፥ ለስ​ም​ህም እዘ​ም​ራ​ለሁ።

50 የን​ጉ​ሡን መድ​ኀ​ኒት ታላቅ ያደ​ር​ጋ​ታል፥ ቸር​ነ​ቱ​ንም ለቀ​ባው ለዳ​ዊት፥ ለዘ​ሩም እስከ ዘለ​ዓ​ለም ያደ​ር​ጋል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos