Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሰባ​ተ​ኛው ራእይ

1 በሦ​ስ​ተ​ኛ​ውም ቀን በዛፍ ሥር ተቀ​ምጬ ሳለሁ፦

2 ከዚ​ያች ዛፍ ፊት ለፊት ቃል መጣ፤ “ዕዝራ! ዕዝራ!” ብሎ ጠራኝ፤ እኔም፥ “እነ​ሆኝ ጌታ ሆይ፥” አልሁ፤ ተነ​ሥ​ቼም ቆምሁ፤

3 እር​ሱም እን​ዲህ አለኝ፥ “ለሙሴ ፈጽሜ ታየ​ሁት፤ ወገ​ኖ​ችም ለግ​ብፅ በተ​ገዙ ጊዜ ጳጦስ በሚ​ባል እን​ጨት ሥር ተና​ገ​ር​ሁት።

4 ላክ​ሁ​ትም፤ ወገ​ኖ​ች​ንም ከግ​ብፅ አወ​ጣ​ኋ​ቸው፤ ሙሴ​ንም ወደ ደብረ ሲና ወሰ​ድ​ሁት፤ ብዙ ቀንም በእኔ ዘንድ አኖ​ር​ሁት።

5 ብዙ ድን​ቅን ነገ​ር​ሁት፤ የዘ​መ​ና​ት​ንም ምሥ​ጢር አሳ​የ​ሁት፤ ኋለ​ኛ​ው​ንም ዘመን ነገ​ር​ሁት።

6 ይህን ነገር ተና​ገር፤ ይህ​ንም ነገር ሰውር ብዬ አዘ​ዝ​ሁት።

7 አሁ​ንም ለአ​ንተ እል​ሃ​ለሁ፦

8 የነ​ገ​ር​ሁ​ህን ያን ነገር ታውቅ ዘንድ፥ ያየ​ኸው ሕል​ም​ህ​ንም፥ የሰ​ማ​ኸ​ውን ትር​ጓ​ሜ​ው​ንም በል​ቡ​ናህ ጠብ​ቀው።

9 ከሰው ለይ​ተው ይወ​ስ​ዱ​ሃ​ልና፥ ከዚ​ህም በኋላ ዓለም እስ​ኪ​ያ​ልፍ ድረስ እን​ዳ​ንተ ያሉት ባሉ​በት ቦታ ከል​ጆች ጋር ትኖ​ራ​ለህ።

10 የዓ​ለም የጐ​ል​ማ​ሳ​ነቱ ወራት አል​ፏ​ልና፥ ዘመ​ኑም አር​ጅ​ት​ዋ​ልና።

11 ዓለም ለዐ​ሥር ክፍል ተከ​ፍ​ሏ​ልና እስከ ዐሥ​ርም ድረስ ደር​ሷ​ልና።

12 የዐ​ሥ​ረ​ኛው እኩ​ሌታ ቀር​ት​ዋ​ልና።

13 አሁን ግን ቤት​ህን አዘ​ጋጅ፤ አዘ​ን​ተ​ኞ​ቻ​ቸ​ው​ንም ደስ አሰ​ኛ​ቸው፤ ዐዋ​ቆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ልብ አስ​ደ​ር​ጋ​ቸው፤ እን​ግ​ዲህ የም​ታ​ልፍ ሕይ​ወ​ት​ንም ተዋት።

14 መዋቲ አሳ​ብን እን​ግ​ዲህ ተወው፤ የሰው ሸክ​ም​ንም ከላ​ይህ ጣል፤ የሚ​ሞት አሳ​ብ​ንም ተው፤ የማ​ይ​ሞ​ተ​ው​ንም ልበስ፤ እን​ግ​ዲ​ህም ወዲህ ከዚህ ዓለም ትሸ​ጋ​ገር ዘንድ አፍ​ጥን።

15 ይች ያየ​ሃት ክፋት ዛሬ ደር​ሳ​ለ​ችና፤ እን​ግ​ዲህ ወዲህ ከእ​ርሷ የም​ት​ከፋ ዳግ​መኛ ትደ​ረ​ጋ​ለ​ችና።

16 ዓለም እያ​ረ​ጀና እየ​ደ​ከመ በሚ​ሄድ መጠን እን​ዲሁ በው​ስጡ የሚ​ኖሩ ክፋ​ታ​ቸው ትበ​ዛ​ለ​ችና።

17 እው​ነት ትጠ​ፋ​ለ​ችና፥ አሰ​ትም ትጸ​ና​ለ​ችና። ይህ ያየ​ኸ​ውም ንስር ይደ​ርስ ዘንድ ይቸ​ኵ​ላ​ልና።”

18 እኔም መለ​ስ​ሁ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አል​ሁት፥ “እን​ግ​ዲ​ህስ ወዲህ በፊ​ትህ እና​ገ​ራ​ለሁ።

19 አቤቱ፥ እኔ እሄ​ዳ​ለ​ሁና፥ እንደ አዘ​ዝ​ኸ​ኝም ዛሬ ያሉ​ትን ሕዝብ አስ​ተ​ም​ራ​ቸ​ዋ​ለ​ሁና። እን​ግ​ዲህ ወዲህ ዳግ​መኛ የሚ​ወ​ለ​ዱ​ትን ማን ያስ​ተ​ም​ራ​ቸ​ዋል?

20 ዓለም በጨ​ለማ ውስጥ አለና፤ በው​ስጡ ለሚ​ኖ​ሩ​ትም ብር​ሃን የላ​ቸ​ውም።

21 ኦሪ​ትህ ተቃ​ጥ​ላ​ለ​ችና፥ የሠ​ራ​ኸ​ውን፥ ትሠ​ራ​ውም ዘንድ ያለ​ህን የሚ​ያ​ው​ቀው የለ​ምና።

22 በፊ​ት​ህስ ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን ካገ​ኘሁ፥ ቅዱስ መን​ፈ​ስ​ህን ላክ​ልኝ፤ እኔም ሰው የሕ​ይ​ወት መን​ገ​ድን ማግ​ኘት ይችል ዘንድ፥ ሊኖሩ የሚ​ወ​ድዱ ሰዎ​ችም ይድኑ ዘንድ ከጥ​ንት ጀምሮ በዓ​ለም የሆ​ነ​ውን ሁሉና በኦ​ሪ​ትህ ውስጥ ተጽፎ ያለ​ውን እጽ​ፋ​ለሁ።”

23 እር​ሱም መለ​ሰ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ሄደህ ወገ​ኖ​ች​ህን ሰብ​ስ​ባ​ቸው፤ እስከ አርባ ቀንም ድረስ እን​ዳ​ይ​ፈ​ል​ጉህ ንገ​ራ​ቸው።

24 አንተ ግን ብዙ ብራና አዘ​ጋጅ፥ ከአ​ን​ተም ጋራ ሶር​ያን፥ ደር​ብ​ያን፥ ሰላ​ም​ያን፥ ኢቀ​ና​ን​ንና አሳ​ሄ​ልን እኒ​ህን አም​ስ​ቱን ሰዎች ውሰ​ዳ​ቸው። እነ​ርሱ በመ​ጻፍ ጠቢ​ባን ናቸ​ውና።

25 ወደ​ዚህ ና፤ በል​ቡ​ና​ህም የጥ​በብ መብ​ራ​ትን አበ​ራ​ለሁ፤ ትጽ​ፍም ዘንድ ያለ​ህን ሁሉ እስ​ክ​ት​ጨ​ርስ ድረስ እን​ግ​ዲህ አት​ጠ​ፋም።

26 በጨ​ረ​ስህ ጊዜ ግልጥ የም​ታ​ደ​ር​ገው አለ፤ የም​ት​ሠ​ው​ረ​ውም አለ፤ ለዐ​ዋ​ቂ​ዎ​ችም፥ ለጠ​ቢ​ባ​ንም ትሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለህ፤ ነገ በዚህ ሰዓት ትጽፍ ዘንድ ትጀ​ም​ራ​ለህ።”

27 እንደ አዘ​ዘ​ኝም ሄጄ ሕዝ​ቡን ሁሉ ሰበ​ሰ​ብሁ።

28 እን​ዲ​ህም አል​ኋ​ቸው፥ “እስ​ራ​ኤል፥ ይህን ነገር ስሙ።

29 አባ​ቶ​ቻ​ችሁ ቀድሞ በግ​ብጽ ምድር ኖሩ፤ ከዚ​ያም ተቤ​ዣ​ቸው።

30 የሕ​ይ​ወት ሕግ​ንም ተቀ​በሉ፤ ግን አል​ጠ​በ​ቁም፤ ከእ​ነ​ር​ሱም በኋላ ያላ​ች​ሁት እና​ንተ ካዳ​ች​ሁት።

31 ምድረ ርስ​ትን ሰጠን፤ የጽ​ዮ​ን​ንም ምድር አወ​ረ​ሰን፤ እና​ን​ተም፥ አባ​ቶ​ቻ​ች​ሁም ካዳ​ች​ሁት፤ እር​ሱ​ንም መበ​ደል አል​ተ​ዋ​ች​ሁም፤ የአ​ዘ​ዛ​ችሁ የል​ዑል መን​ገ​ድን አል​ጠ​በ​ቃ​ች​ሁም።

32 እርሱ እው​ነት ፈራጅ ነውና በጊ​ዜው የሰ​ጣ​ች​ሁን ቀማ​ችሁ።

33 አሁ​ንም እና​ንተ በዚህ አላ​ችሁ፤ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችሁ ግን ከእ​ና​ንተ ተለ​ይ​ተው በው​ስጥ ናቸው።

34 ልቡ​ና​ች​ሁን ያስ​ገ​ዛ​ች​ሁት፥ ሕሊ​ና​ች​ሁ​ንም የገ​ሠ​ጻ​ች​ሁት እንደ ሆነ፥ ሕይ​ወ​ታ​ች​ሁ​ንም የጠ​በ​ቃ​ች​ሁት እንደ ሆነ አት​ሞ​ቱም።

35 ከሞት በኋላ ፍርድ ይመ​ጣ​ልና፥ እኛ​ንም በሕ​ይ​ወት አያ​ኖ​ረ​ን​ምና፥ ያን​ጊ​ዜም የጻ​ድ​ቃን ስማ​ቸው ይገ​ለ​ጣል፤ የኃ​ጥ​ኣ​ንም ሥራ​ቸው ይገ​ለ​ጣል።

36 ከእ​ና​ንተ ወደ እኔ የሚ​መጣ አይ​ኑር፤ እስከ አርባ ቀንም ድረስ አት​ፈ​ል​ጉኝ።”

37 እን​ዳ​ዘ​ዘ​ኝም እነ​ዚ​ያን አም​ስ​ቱን ሰዎች ይዤ ወደ ምድረ በዳው ሄድን፤ በዚ​ያም ተቀ​መ​ጥን።

38 በማ​ግ​ሥ​ቱም ቃል መጣ፥ “ዕዝራ! ዕዝራ!” ብሎ ጠርቶ እን​ዲህ አለኝ፥ “አፍ​ህን ክፈት እኔም የማ​ጠ​ጣ​ህን ጠጣ።”

39 አፌ​ንም በከ​ፈ​ትሁ ጊዜ ውኃ የተ​መላ፥ መልኩ እሳት የሚ​መ​ስል መጠ​ጥን አጠ​ጣኝ።

40 ተቀ​ብ​ዬም ጠጣ​ሁት፤ ልቡ​ና​ዬም ፈጽሞ ዕው​ቀ​ትን ተና​ገረ፤ ዕው​ቀ​ትም በል​ቡ​ናዬ በዛ፤ ነፍ​ሴም ትጠ​ብ​ቀ​ዋ​ለች፤ ታስ​በ​ዋ​ለ​ችም።

41 አፌም ተከ​ፈተ፤ ከዚ​ያም ወዲያ ዝም አላ​ለም።

42 ልዑ​ልም ለእ​ነ​ዚያ ለአ​ም​ስቱ ሰዎች ጥበ​ብን ሰጣ​ቸው፤ የማ​ያ​ው​ቁ​ት​ንም ምል​ክት የሆ​ነ​ውን ይህን ሁሉ በማ​ከ​ታ​ተል ጻፉ፤ በዚ​ያም አርባ ቀን ተቀ​መጡ፤ እነ​ር​ሱም ቀን ቀን ይጽፉ ነበር፤ ማታ ማታም እህል ይመ​ገቡ ነበር፤

43 እኔ ግን ቀን እና​ገ​ራ​ለሁ፤ ሌሊ​ትም ዝም አል​ልም።

44 በእ​ነ​ዚያ በአ​ርባ ቀኖ​ችም ሃያ አራት መጻ​ሕ​ፍት ተጻፉ።

45 ከዚ​ህም በኋላ እነ​ዚያ አርባ ቀኖች በተ​ፈ​ጸሙ ጊዜ ልዑል ተና​ገ​ረኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “አስ​ቀ​ድሞ የጻ​ፋ​ች​ሁ​ትን ያን ግልጥ አድ​ር​ገው፤ የሚ​ገ​ባ​ውም የማ​ይ​ገ​ባ​ውም ሁሉ ያን​ብ​በው።

46 ይህን ግን ለጠ​ቢ​ባን ሕዝብ ትሰ​ጣ​ቸው ዘንድ ጠብቅ።

47 በእ​ነ​ዚህ ውስጥ የማ​ስ​ተ​ዋል መብ​ራት፥ የጥ​በብ ምንጭ፥ የዕ​ው​ቀ​ትም ፈሳሽ አለና።”

48 እን​ዲ​ሁም አደ​ረ​ግሁ፤ በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት፥ ከዓ​መ​ታቱ ሱባ​ዔ​ያት በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ፥ ከፍ​ጥ​ረተ ዓለም በኋላ በአ​ም​ስት ሺህ ዓመ​ታት፥ ጨረቃ ሠርቅ ባደ​ረ​ገች በዐ​ሥ​ረ​ኛው ቀን በሦ​ስ​ተ​ኛው ወር፥ በዘ​ጠና አንድ ቀናት።

49 ያን​ጊዜ ይህን ሁሉ ከጻፈ በኋላ ዕዝ​ራን ይዘው እንደ እርሱ ያሉ ሰዎች ወዳ​ሉ​በት ሀገር ወሰ​ዱት፤ እር​ሱም እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ የል​ዑል የጥ​በቡ ጸሓፊ ተባለ። የዕ​ዝራ መጽ​ሐፍ ተፈ​ጸመ፤ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋና ይግ​ባው፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ አሜን።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች