La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘፀአት 2:22 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ያችም ሴት ፀነ​ሰች፤ ወንድ ልጅም ወለ​ደች፤ ሙሴም፥ “በሌላ ምድር መጻ​ተኛ ነኝ” ሲል ስሙን ጌር​ሳም ብሎ ጠራው። ዳግ​መ​ኛም ፀነ​ሰች፤ ወንድ ልጅም ወለ​ደች፤ ስሙ​ንም ኤል​ኤ​ዜር አለው፤ የአ​ባቴ ፈጣሪ ረዳቴ ነው ሲል።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሲፓራም ወንድ ልጅ ወለደች፤ ሙሴም፣ “በባዕድ አገር መጻተኛ ነኝ” ሲል የልጁን ስም ጌርሳም ብሎ ጠራው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ወንድ ልጅም ወለደች፦ “በሌላ ምድር መጻተኛ ነኝ” ሲል ስሙን “ጌርሾም” ብሎ ጠራው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

እርስዋም ወንድ ልጅ ወለደችለት፤ ሙሴም “እኔ በዚህ ምድር መጻተኛ ነኝ” ሲል ልጁን ጌርሾም ብሎ ጠራው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ወንድ ልጅም ወለደች፤ “በሌላ ምድር መጻተኛ ነኝ” ሲል ስሙን ጌርሳም ብሎ ጠራው።

Ver Capítulo



ዘፀአት 2:22
15 Referencias Cruzadas  

“እኔ በእ​ና​ንተ ዘንድ ስደ​ተ​ኛና መጻ​ተኛ ነኝ፤ በእ​ና​ንተ ዘንድ እን​ድ​ገዛ የመ​ቃ​ብር ርስት ስጡኝ፤ ሬሳ​ዬ​ንም እንደ እና​ንተ ልቅ​በር።”


ከሕ​ዝብ ወደ ሕዝብ፥ ከመ​ን​ግ​ሥ​ትም ወደ ሌላ ሕዝብ አለፉ።


አባ​ቶ​ቻ​ችን ስደ​ተ​ኞች እንደ ነበሩ እኛ በፊ​ትህ ስደ​ተ​ኞ​ችና መጻ​ተ​ኞች ነን፤ ዘመ​ና​ች​ንም በም​ድር ላይ እንደ ጥላ ናት፤ አት​ጸ​ና​ምም።


ቍጥር የሌ​ላት ክፋት አግ​ኝ​ታ​ኛ​ለ​ችና፤ ኀጢ​አ​ቶቼ ተገ​ና​ኙኝ፥ ማየ​ትም ተስ​ኖ​ኛል፤ ከራሴ ጠጕር ይልቅ በዙ፥ ልቤም ተወኝ።


ሕፃ​ኑም በአ​ደገ ጊዜ ወደ ፈር​ዖን ልጅ ወሰ​ደ​ችው፤ ለእ​ር​ስ​ዋም ልጅ ሆነ​ላት። እኔ ከውኃ አው​ጥ​ቼ​ዋ​ለ​ሁና ስት​ልም ስሙን ሙሴ ብላ ጠራ​ችው ።


እና​ንተ በግ​ብፅ ምድር ስደ​ተ​ኞች ነበ​ራ​ች​ሁና ስደ​ተ​ኛ​ውን አት​በ​ድ​ሉት፤ ግፍም አታ​ድ​ር​ጉ​በት።


ሙሴም ሚስ​ቱ​ንና ልጆ​ቹን ወሰደ፤ በአ​ህ​ዮች ላይም አስ​ቀ​መ​ጣ​ቸው፤ ወደ ግብ​ፅም ሀገር ተመ​ለሰ፤ ሙሴም ያችን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በትር በእጁ ይዞ ሄደ።


“ምድ​ርም ለእኔ ናትና፥ እና​ን​ተም በእኔ ፊት እን​ግ​ዶ​ችና መጻ​ተ​ኞች ናች​ሁና ምድ​ርን ለዘ​ለ​ዓ​ለም አት​ሽጡ።


ስለ​ዚ​ህም ነገር ሙሴ ኮብ​ልሎ በም​ድ​ያም ሀገር ስደ​ተኛ ሆኖ ኖረ፤ በዚ​ያም ሁለት ልጆ​ችን ወለደ።


የዳ​ንም ልጆች የተ​ቀ​ረ​ፀ​ውን የሚ​ካን ምስል ለራ​ሳ​ቸው አቆሙ፤ የሙ​ሴም ልጅ የጌ​ር​ሳም ልጅ ዮና​ታን፥ እር​ሱና ልጆቹ እስከ ሀገ​ራ​ቸው ምርኮ ድረስ ለዳን ነገድ ካህ​ናት ነበሩ።


የመ​ው​ለ​ጃ​ዋም ወራት በደ​ረሰ ጊዜ ሐና ወንድ ልጅ ወለ​ደች፤ እር​ስ​ዋም፥ “ከሠ​ራ​ዊት ጌታ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለም​ኜ​ዋ​ለሁ” ስትል ስሙን “ሳሙ​ኤል” ብላ ጠራ​ችው።