La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘፍጥረት 48:9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ዮሴ​ፍም ለአ​ባቱ ፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዚህ የሰ​ጠኝ ልጆች ናቸው” አለው። ያዕ​ቆ​ብም፥ “እባ​ር​ካ​ቸው ዘንድ ወደ እኔ አቅ​ር​ብ​ልኝ” አለው።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ዮሴፍም፣ “እነዚህ እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ናቸው” ብሎ ለአባቱ መለሰለት። እስራኤልም፣ “አቅርባቸውና ልመርቃቸው” አለ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ዮሴፍም ለአባቱ፦ “እግዚአብሔር በዚህ የሰጠኝ ልጆቼ ናቸው” አለ። እርሱም፦ “እባርካቸው ዘንድ ወደዚህ አቅርብልኝ” አለ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ዮሴፍም “እነዚህ እግዚአብሔር በዚህ አገር ሳለሁ የሰጠኝ የእኔ ልጆች ናቸው” ብሎ ለአባቱ መለሰለት። ያዕቆብም “እባርካቸው ዘንድ ወደ እኔ አቅርብልኝ” አለው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ዮሴፍም ለአባቱ፦ እግዚአብሔር በዚህ የሰጠኝ ልጆቼ ናቸው አለ። እርሱም፦ እባርካቸው ዘንድ ወደዚህ አቅርብልኝ አለ።

Ver Capítulo



ዘፍጥረት 48:9
18 Referencias Cruzadas  

ሳል​ሞ​ትም ነፍሴ እን​ድ​ት​ባ​ር​ክህ እኔ እን​ደ​ም​ወ​ደው መብል አዘ​ጋ​ጅ​ተህ እበላ ዘንድ አም​ጣ​ልኝ።”


ያዕ​ቆ​ብም፥ “የማ​ኅ​ፀ​ን​ሽን ፍሬ የም​ከ​ለ​ክ​ልሽ እኔ እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነኝን?” ብሎ ራሔ​ልን ተቈ​ጣት።


ዔሳ​ውም ዐይ​ኑን አነ​ሣና ሴቶ​ች​ንና ልጆ​ችን አየ፤ እን​ዲ​ህም አለ፥ “እነ​ዚህ ምኖ​ችህ ናቸው?” እር​ሱም፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለእኔ ለአ​ገ​ል​ጋ​ይህ የሰ​ጠኝ ልጆች ናቸው” አለ።


እነ​ዚ​ህም ሁሉ ዐሥራ ሁለቱ የያ​ዕ​ቆብ ልጆች ናቸው፤ አባ​ታ​ቸ​ውም ይህን ነገር ነገ​ራ​ቸው፤ ባረ​ካ​ቸ​ውም፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ው​ንም እንደ በረ​ከ​ታ​ቸው ባረ​ካ​ቸው።


እነ​ዚህ ሁሉ ቀንደ መለ​ከ​ቱን ከፍ ያደ​ርጉ ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል በን​ጉሡ ፊት የሚ​ዘ​ም​ረው የኤ​ማን ልጆች ነበሩ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለኤ​ማን ዐሥራ አራት ወን​ዶች ልጆ​ች​ንና ሦስት ሴቶች ልጆ​ችን ሰጠው።


ሚስ​ትህ በቤ​ትህ እል​ፍኝ ውስጥ እን​ደ​ሚ​ያ​ፈራ ወይን ትሆ​ና​ለች፤ ልጆ​ች​ህም በማ​ዕ​ድህ ዙሪያ እንደ አዲስ የወ​ይራ ተክል ይሆ​ናሉ።


እነሆ፥ እኔና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሰ​ጠኝ ልጆች ለእ​ስ​ራ​ኤል በጽ​ዮን ተራራ ከሚ​ኖ​ረው ከሠ​ራ​ዊት ጌታ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ምል​ክ​ትና ተአ​ም​ራት ነን።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው ሙሴ ሳይ​ሞት የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች የባ​ረ​ከ​ባት በረ​ከት ይህች ናት።


ያዕ​ቆ​ብም በሚ​ሞ​ት​በት ጊዜ የዮ​ሴ​ፍን ልጆች እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ውን በእ​ም​ነት ባረ​ካ​ቸው፤ በበ​ትሩ ጫፍም ሰገደ።


የመ​ው​ለ​ጃ​ዋም ወራት በደ​ረሰ ጊዜ ሐና ወንድ ልጅ ወለ​ደች፤ እር​ስ​ዋም፥ “ከሠ​ራ​ዊት ጌታ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለም​ኜ​ዋ​ለሁ” ስትል ስሙን “ሳሙ​ኤል” ብላ ጠራ​ችው።


ስለ​ዚህ ልጅ ተሳ​ልሁ፤ ጸለ​ይ​ሁም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የለ​መ​ን​ሁ​ትን ልመ​ና​ዬን ሰጥ​ቶ​ኛል፤