La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ምሳሌ 13:22 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ደግ ሰው ለልጅ ልጅ ያወርሳል፥ የኀጢአተኞች ብልጽግና ግን ለጻድቃን ይደልባል።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ደግ ሰው ለልጅ ልጆቹ ውርስ ትቶ ያልፋል፤ የኀጢአተኞች ሀብት ግን ለጻድቃን ይከማቻል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ጻድቅ ሰው ለልጅ ልጆቹ ያወርሳል፥ የኃጢአተኛ ብልጥግና ግን ለጻድቅ ትጠበቃለች።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ደግ ሰው ለልጅ ልጆቹ የሚተላለፍ ሀብት ያገኛል፤ የኃጢአተኞችን ሀብት ግን ቅን ሰዎች ይወርሱታል።

Ver Capítulo



ምሳሌ 13:22
11 Referencias Cruzadas  

አሁ​ንም ትበ​ረቱ ዘንድ፥ የም​ድ​ሩ​ንም ፍሬ ትበሉ ዘንድ፥ ልጆ​ቻ​ች​ሁም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይወ​ር​ሱ​አት ዘንድ፥ ሴቶ​ችን ልጆ​ቻ​ች​ሁን ለወ​ን​ዶች ልጆ​ቻ​ቸው አት​ስጡ፤ ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ለወ​ን​ዶች ልጆ​ቻ​ችሁ አት​ው​ሰዱ፤ ሰላ​ማ​ቸ​ው​ንና ደኅ​ን​ነ​ታ​ቸ​ው​ንም ለዘ​ለ​ዓ​ለም አትሹ።


ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስሙ ቡሩክ ይሁን።


በሰ​ገ​ነት ላይ እንደ በቀለ ሣር፥ ሳይ​ነ​ቀል እን​ደ​ሚ​ደ​ርቅ፥


የሽማግሌዎች አክሊል የልጅ ልጆች ናቸው፤ የልጆችም ክብር አባቶቻቸው ናቸው።


እርሱ በፊቱ ደግ ለሆነ ሰው ጥበ​ብ​ንና ዕው​ቀ​ትን፥ ደስ​ታ​ንም ይሰ​ጠ​ዋል፤ ለኀ​ጢ​አ​ተኛ ግን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ደግ ለሆነ ይሰጥ ዘንድ እን​ዲ​ሰ​በ​ስ​ብና እን​ዲ​ያ​ከ​ማች ጥረ​ትን ይሰ​ጠ​ዋል። ይህ ደግሞ ከንቱ፥ ነፋ​ስ​ንም እንደ መከ​ተል ነው።