Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 128 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የመ​ዓ​ርግ መዝ​ሙር።

1 እስ​ራ​ኤል እን​ዲህ ይበል፥ “ከት​ን​ሽ​ነቴ ጀምሮ ሁል​ጊዜ ተሰ​ለ​ፉ​ብኝ፤

2 ከት​ን​ሽ​ነቴ ጀምሮ ሁል​ጊዜ ተሰ​ለ​ፉ​ብኝ፤ ነገር ግን አል​ቻ​ሉ​ኝም።

3 ኃጥ​ኣን በጀ​ር​ባዬ ላይ መቱኝ፥ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንም አበ​ዙ​አት።”

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጻድቅ ነው፤ የኃ​ጥ​ኣ​ንን አን​ገ​ታ​ቸ​ውን ቈረጠ።

5 ጽዮ​ንን የሚ​ጠሉ ሁሉ ይፈሩ፥ ወደ ኋላ​ቸ​ውም ይመ​ለሱ።

6 በሰ​ገ​ነት ላይ እንደ በቀለ ሣር፥ ሳይ​ነ​ቀል እን​ደ​ሚ​ደ​ርቅ፥

7 ለሚ​ያ​ጭ​ደው እጁን፥ ነዶ​ዎ​ቹን ለሚ​ሰ​በ​ስ​ብም እቅ​ፉን እን​ደ​ማ​ይ​ሞላ ይሁኑ።

8 በመ​ን​ገ​ድም የሚ​ያ​ልፉ፥ “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በረ​ከት በእ​ና​ንተ ላይ ይሁን፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም እን​መ​ር​ቃ​ች​ኋ​ለን” አይ​በሉ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos