La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኤርምያስ 32:5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ሴዴ​ቅ​ያ​ስም ወደ ባቢ​ሎን ይገ​ባል፤ እኔም እስ​ክ​ጐ​በ​ኘው ድረስ በዚያ ይኖ​ራል፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ ከከ​ለ​ዳ​ው​ያን ጋር ብቷጉ ምንም አይ​ቀ​ና​ች​ሁም።”

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሴዴቅያስንም ወደ ባቢሎን ይወስደዋል፤ በፍርዴ እስከምጐበኘውም ድረስ በዚያ ይቈያል፤ ይላል እግዚአብሔር፤ ከባቢሎናውያን ጋራ ብትዋጉ አይሳካላችሁም” ይላል’ ትላለህ።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እርሱም ሴዴቅያስን ወደ ባቢሎን ያፈልሰዋል፥ እኔም እስክጐበኘው ድረስ በዚያ ይኖራል፥ ይላል ጌታ፤ ከከላዳውያን ጋር ብትዋጉ ምንም አይቀናችሁም’?”

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ሴዴቅያስ ወደ ባቢሎን ይወሰዳል፤ እኔ በሞት እስክጐበኘው ድረስ በዚያ ይኖራል፤ ከባቢሎናውያን ጋር ለመዋጋት ቢሞክር እንኳ አይሳካለትም፤ እኔ እግዚአብሔር ይህን ተናግሬአለሁ።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

እርሱም ሴዴቅያስን ወደ ባቢሎን ያፈልሰዋል፥ እኔም እስክጐበኘው ድረስ በዚያ ይኖራል፥ ይላል እግዚአብሔር፥ ከከላዳውያን ጋር ብትዋጉ ምንም አትረቡም።

Ver Capítulo



ኤርምያስ 32:5
20 Referencias Cruzadas  

እነ​ሆም፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእኛ ላይ አለቃ ነው፤ መለ​ከ​ቱ​ንም የሚ​ነፉ ካህ​ናቱ ከእኛ ጋር ናቸው፤ በእ​ና​ን​ተም ላይ ይጮ​ኻሉ። የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ሆይ፥ አይ​በ​ጃ​ች​ሁ​ምና ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ አም​ላክ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጋር አቷጉ።”


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መን​ፈስ በካ​ህኑ በኢ​ዮ​አዳ ልጅ በአ​ዛ​ር​ያስ ላይ መጣ፤ እር​ሱም በሕ​ዝቡ ፊት ቆመና፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ ለምን ትተ​ላ​ለ​ፋ​ላ​ችሁ? መል​ካ​ምም አይ​ሆ​ን​ላ​ች​ሁም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስለ ተዋ​ችሁ እርሱ ትቶ​አ​ች​ኋል” አላ​ቸው።


ጥበብና ብርታት፥ ምክርም፥ በኃጥእ ዘንድ የሉም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ተስ​ፋ​ሽን አስ​ቈ​ር​ጦ​ሻ​ልና፥ በእ​ር​ሱም አይ​ከ​ና​ወ​ን​ል​ሽ​ምና እጅ​ሽን በራ​ስሽ ላይ አድ​ር​ገሽ ከዚያ ደግሞ ትወ​ጫ​ለሽ።


ወደ ባቢ​ሎን ይወ​ሰ​ዳሉ፤ እስ​ከ​ም​ጐ​በ​ኛ​ቸው ቀን ድረስ በዚያ ይኖ​ራሉ፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ በዚ​ያን ጊዜም ትወ​ጣ​ላ​ችሁ፤ ወደ​ዚ​ህም ስፍራ ትመ​ለ​ሳ​ላ​ችሁ።”


አሕ​ዛ​ብም መጥ​ተው ይህ​ችን ሀገር ያዟት፤ ይህ​ችም ከተማ ከረ​ኃ​ቡና ከጦሩ የተ​ነሣ በወ​ጓት በከ​ለ​ዳ​ው​ያን ሰዎች እጅ ወደ​ቀች፤ እንደ ተና​ገ​ር​ኸ​ውም ሆነ።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ወደ ኤር​ም​ያስ እን​ዲህ ሲል መጣ፦


የከ​ለ​ዳ​ው​ያን ተዋ​ጊ​ዎች ለመ​ዋ​ጋት መጥ​ተ​ዋል፤ ነገር ግን በቍ​ጣ​ዬና በመ​ዓቴ በገ​ደ​ል​ኋ​ቸው ሰዎች ሬሳ​ዎች እሞ​ላ​ታ​ለሁ፥ ስለ ክፋ​ታ​ቸው ሁሉ ፊቴን ከዚ​ህች ከተማ እመ​ል​ሳ​ለሁ።


ነገር ግን እና​ን​ተን የሚ​ወ​ጉ​ትን የከ​ለ​ዳ​ው​ያ​ንን ጭፍራ ሁሉ ብት​መቱ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጥቂት ተወ​ግ​ተው ያል​ሞቱ ቢቀሩ ሁሉ እያ​ን​ዳ​ንዱ በስ​ፍ​ራው ይነ​ሣሉ፤ ይህ​ቺ​ንም ሀገር በእ​ሳት ያቃ​ጥ​ላሉ።”


የይ​ሁዳ ንጉሥ ሴዴ​ቅ​ያ​ስና ሰል​ፈ​ኞ​ቹም ሁሉ በአ​ዩ​አ​ቸው ጊዜ፥ በሌ​ሊት ሸሹ፤ በን​ጉ​ሡም አት​ክ​ልት መን​ገድ በሁ​ለቱ ቅጥር መካ​ከል በነ​በ​ረው ደጅ ከከ​ተ​ማ​ዪቱ ወጡ፤ በዓ​ረ​ባም መን​ገድ ወጡ።


የከ​ለ​ዳ​ው​ያ​ንም ሠራ​ዊት ተከ​ታ​ተ​ላ​ቸው፤ ሴዴ​ቅ​ያ​ስ​ንም በኢ​ያ​ሪኮ ሜዳ አገ​ኙት፤ ይዘ​ውም በሐ​ማት ምድር ወዳ​ለ​ችው ወደ ዴብ​ላታ ወደ ባቢ​ሎን ንጉሥ ወደ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር አመ​ጡት፤ እር​ሱም ፍር​ድን በእ​ርሱ ላይ ተና​ገረ።


የሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስ​ንም ዐይን አወጣ፤ በሰ​ን​ሰ​ለ​ትም አስሮ ወደ ባቢ​ሎን ወሰ​ደው።


ኖን። በእጄ ስለ​ተ​ታቱ ኀጢ​አ​ቶች ተጋ፤ በአ​ን​ገቴ ላይ ወጥ​ተ​ዋል፤ ጕል​በቴ ደከመ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ልቋ​ቋ​መው በማ​ል​ች​ለው መከራ እጅ ሰጥ​ቶ​ኛ​ልና።


በመ​ካ​ከ​ላ​ቸ​ውም የሚ​ኖ​ረው አለቃ በት​ከ​ሻው ላይ አን​ግቶ በጨ​ለማ ይወ​ጣል፤ በዚያ ያወጡ ዘንድ ግን​ቡን ይነ​ድ​ላሉ፤ በዐ​ይ​ኑም ምድ​ርን እን​ዳ​ያይ ፊቱን ይሸ​ፍ​ናል።


መረ​ቤ​ንም በእ​ርሱ ላይ እዘ​ረ​ጋ​ለሁ፤ በወ​ጥ​መ​ዴም ይያ​ዛል፤ ወደ ከለ​ዳ​ው​ያ​ንም ምድር ወደ ባቢ​ሎን አመ​ጣ​ዋ​ለሁ፤ ሆኖም አያ​ያ​ትም፤ በዚ​ያም ይሞ​ታል።


እርሱ ግን በእ​ርሱ ላይ ሸፈተ፤ ፈረ​ሶ​ች​ንና ብዙ​ንም ሕዝብ ይሰ​ጡት ዘንድ መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ወደ ግብፅ ላከ። በውኑ ይከ​ና​ወ​ን​ለት ይሆን? ይህ​ንስ ያደ​ረገ ያመ​ል​ጣ​ልን? ቃል ኪዳ​ን​ንስ ያፈ​ረሰ ያመ​ል​ጣ​ልን?


ሙሴም አለ፥ “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ ለምን ትተ​ላ​ለ​ፋ​ላ​ችሁ? ይህ ለእ​ና​ንተ መል​ካም አይ​ደ​ለም።