La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ነገሥት 9:36 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ተመ​ል​ሰ​ውም ለኢዩ ነገ​ሩት፤ እር​ሱም፥ “በባ​ሪ​ያው በቴ​ስ​ብ​ያ​ዊው ኤል​ያስ እጅ በኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤል እርሻ የኤ​ል​ዛ​ቤ​ልን ሥጋ ውሾች ይበ​ላሉ፥

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ተመልሰውም ይህን ሲነግሩት፣ ኢዩ እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔር ለባሪያው ለቴስብያዊው ለኤልያስ፣ በኢይዝራኤል ምድር ዕርሻ ውስጥ ውሾች የኤልዛቤልን ሥጋ ይበሉታል፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ይህንንም ሁሉ ለኢዩ በነገሩት ጊዜ ኢዩ እንዲህ አለ፤ “ይህ ሁሉ የተፈጸመው እግዚአብሔር በአገልጋዩ ቴስቢያዊው በኤልያስ አማካይነት አስቀድሞ በተናገረው መሠረት ነው፤ ይኸውም ‘የኤልዛቤልም ሬሳ በኢይዝራኤል ግዛት ውሾች ይበሉታል፤

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ይህንንም ሁሉ ለኢዩ በነገሩት ጊዜ ኢዩ እንዲህ አለ፤ “ይህ ሁሉ የተፈጸመው እግዚአብሔር በአገልጋዩ ቴስቢያዊው በኤልያስ አማካይነት አስቀድሞ በተናገረው መሠረት ነው፤ ይኸውም ‘የኤልዛቤልም ሬሳ በኢይዝራኤል ግዛት ውሾች ይበሉታል፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ተመልሰውም ነገሩት፤ እርሱም “በባሪያው በቴስብያዊ ኤልያስ ‘በኢይዝራኤል እርሻ የኤልዛቤልን ሥጋ ውሾች ይበላሉ፤

Ver Capítulo



2 ነገሥት 9:36
9 Referencias Cruzadas  

ደግ​ሞም በነ​ቢዩ በና​ታን እጅ ልኮ ስሙን ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፍቁረ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብሎ ጠራው።


የሶ​ር​ያም ንጉሥ አገ​ል​ጋ​ዮች እን​ዲህ አሉት፥ “የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ የተ​ራ​ሮች አም​ላክ ነው እንጂ የሸ​ለቆ አም​ላክ አይ​ደ​ለም፤ ስለ​ዚህ በር​ት​ተ​ው​ብን ነበር፤ ነገር ግን በሜዳ ብን​ዋ​ጋ​ቸው ድል እና​ደ​ር​ጋ​ቸው ነበር።


ኤል​ያ​ስም እንደ ተና​ገ​ረው እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ሞተ።


በጋ​ት​ሔ​ፌር በነ​በ​ረው በአ​ማቴ ልጅ በባ​ሪ​ያው በነ​ቢዩ በዮ​ናስ አፍ እንደ ተና​ገ​ረው እንደ እስ​ራ​ኤል አም​ላክ እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ድን​በር ከሔ​ማት መግ​ቢያ ጀምሮ እስከ ዓረባ ባሕር ድረስ መለሰ።


ለኢዩ፥ “ልጆ​ችህ እስከ አራት ትው​ልድ ድረስ በእ​ስ​ራ​ኤል ዙፋን ላይ ይቀ​መ​ጣሉ” ተብሎ የተ​ነ​ገ​ረው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ይህ ነበረ፤ እን​ዲ​ሁም ሆነ።


ኤል​ዛ​ቤ​ል​ንም በኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤል እርሻ ውሾች ይበ​ሉ​አ​ታል፥ የሚ​ቀ​ብ​ራ​ትም አታ​ገ​ኝም።” በሩ​ንም ከፍቶ ሸሸ።


ሊቀ​ብ​ሩ​አ​ትም በሄዱ ጊዜ ከአ​ና​ቷና ከእ​ግ​ርዋ ተረ​ከዝ ከመ​ዳ​ፍ​ዋም በቀር ምንም አላ​ገ​ኙም።


አሮ​ንና ልጆ​ቹም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሙሴ ያዘ​ዘ​ውን ሁሉ አደ​ረጉ።


ኢያ​ሬ​ዬል፥ ኢያ​ሪ​ቅም፥ ዘቃ​ይ​ንም፤