La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




1 ዜና መዋዕል 1:32 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የአ​ብ​ር​ሃም ዕቅ​ብት ኬጡራ የወ​ለ​ደ​ች​ለት ልጆች፤ ዘም​ራን፥ ዮቅ​ሳን፥ ሜዳም፥ ምድ​ያን፥ ዮሳ​ብቅ፥ ስዌሕ፥ የዮ​ቅ​ሳ​ንም ልጆች፤ ሳባ፥ ዳዳን።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

የአብርሃም ቁባት ኬጡራ የወለደቻቸው ወንዶች ልጆች ዘምራን፣ ዮቅሳን፣ ሜዳን፣ ምድያም፣ የስቦቅና፣ ስዌሕ ናቸው። የዮቅሳን ወንዶች ልጆች፤ ሳባ፣ ድዳን።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

የአብርሃምም ቊባት የኬጡራ ልጆች፤ ዚምራን፥ ዮቅሻን፥ ሜዳን፥ ምድያም፥ የሽቦቅ፥ ሹሐን ናቸው። የዮቅሻንም ልጆች፤ ሳባና ድዳን ናቸው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

አብርሃም ቀጡራ ተብላ ከምትጠራው ቊባቱ ዚምራን፥ ዮቅሻን፥ መዳን፥ ምድያም፥ ዩሽባቅና ሹሐ ተብለው የሚጠሩትን ስድስት ወንዶች ልጆችን ወለደ፤ ዮቅሻንም ሳባና ደዳን ተብለው የሚጠሩትን ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደ፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

የአብርሃምም ቍባት የኬጡራ ልጆች፤ ዘምራን፥ ዮቅሳን፥ ሜዳን፥ ምድያም፥ የስቦቅ፥ ስዌሕ። የዮቅሳንም ልጆች፤ ሳባ፥ ድዳን።

Ver Capítulo



1 ዜና መዋዕል 1:32
19 Referencias Cruzadas  

እነ​ዚያ ይስ​ማ​ኤ​ላ​ው​ያን ነጋ​ዴ​ዎ​ችም ሲያ​ልፉ ወን​ድ​ሞቹ ዮሴ​ፍን ከጕ​ድ​ጓድ ጐት​ተው አወ​ጡት፤ ለይ​ስ​ማ​ኤ​ላ​ው​ያ​ንም ዮሴ​ፍን በሃያ ብር ሸጡት፤ እነ​ር​ሱም ዮሴ​ፍን ወደ ግብፅ ወሰ​ዱት።


የሳ​ባም ንግ​ሥት የሰ​ሎ​ሞ​ንን ስም፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ስም በሰ​ማች ጊዜ ሰሎ​ሞ​ንን በእ​ን​ቆ​ቅ​ልሽ ትፈ​ት​ነው ዘንድ መጣች።


የጡር፥ ናፌስ፥ ቂዳማ፤ እነ​ዚህ የይ​ስ​ማ​ኤል ልጆች ናቸው።


የም​ድ​ያ​ምም ልጆች፤ ጌፌር፥ ዔፌር፥ ሄኖሕ፥ አቢ​ዳን፥ ኤል​ዳን። እነ​ዚህ ሁሉ የኬ​ጡራ ልጆች ነበሩ።


የቴ​ማ​ና​ው​ያ​ንን መን​ገ​ዶች፥ የሳ​ባ​ው​ያ​ንን ክፋ​ትና ቸል​ተ​ኝ​ነት ተመ​ል​ከቱ።


ስለ​ዚህ ሕዝቤ ወደ​ዚህ ይመ​ለ​ሳሉ፤ ፍጹም ጊዜም በላ​ያ​ቸው ይገ​ኛል፤


እን​ደ​ዚህ ብዬ ብና​ገር ኖሮ፥ እነሆ፥ የል​ጆ​ች​ህን ትው​ልድ በበ​ደ​ልሁ ነበር።


ሌሊ​ትም በዲ​ዳ​ና​ው​ያን ጎዳና በዛ​ፎች ውስጥ ታድ​ራ​ለህ፤


የግ​መ​ሎች መንጋ ወደ አንቺ ይመ​ጣሉ፤ የም​ድ​ያ​ምና የኤፋ ግመ​ሎች ይሸ​ፍ​ኑ​ሻል፤ ሁሉ ከሳባ ወር​ቅ​ንና ዕጣ​ንን ይዘው ይመ​ጣሉ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ማዳን ያበ​ሥ​ራሉ።


ድዳ​ን​ንም፥ ቴማ​ን​ንም፥ ሮስ​ንም፥ ፊታ​ቸ​ውን የሚ​ከ​ተ​ቡ​ትን ሁሉ፤


እና​ንተ በድ​ዳን የም​ት​ኖሩ ሆይ! የዔ​ሳ​ውን ጥፋት፥ የም​ጐ​በ​ኝ​በ​ትን ጊዜ አመ​ጣ​በ​ታ​ለ​ሁና ሽሹ፤ ወደ ኋላም ተመ​ለሱ፤ በጥ​ል​ቅም ጕድ​ጓድ ውስጥ ተቀ​መጡ።


ስለ​ዚህ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ እጄን በኤ​ዶ​ም​ያስ ላይ እዘ​ረ​ጋ​ለሁ፤ ከእ​ር​ስ​ዋም ዘንድ ሰው​ንና እን​ስ​ሳን አጠ​ፋ​ለሁ፤ ባድ​ማም አደ​ር​ጋ​ታ​ለሁ፤ ከቴ​ማ​ንና ከድ​ዳ​ንም ያመ​ለጡ በሰ​ይፍ ይወ​ድ​ቃሉ።


ድዳን በተ​መ​ረጡ እን​ስ​ሳ​ትና በሠ​ረ​ገ​ላ​ቸው፥ በክ​ብር ልብ​ስም ነጋ​ዴሽ ነበ​ረች።


እነ​ሆም፥ ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች አንዱ መጥቶ በሙ​ሴና በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ማኅ​በር ሁሉ ፊት ወን​ድ​ሙን ወደ ምድ​ያ​ማ​ዊት ሴት ወሰ​ደው፤ እነ​ር​ሱም በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ዳጃፍ ያለ​ቅሱ ነበር።


“የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች በቀል ምድ​ያ​ማ​ው​ያ​ንን ተበ​ቀል፤ ከዚ​ያም በኋላ ወደ ወገ​ኖ​ችህ ትጨ​መ​ራ​ለህ።”