Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


1 ነገሥት 10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ንግ​ሥተ ሳባ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ያደ​ረ​ገ​ችው ጕዞ
( 2ዜ.መ. 9፥1-12 )

1 የሳ​ባም ንግ​ሥት የሰ​ሎ​ሞ​ንን ስም፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ስም በሰ​ማች ጊዜ ሰሎ​ሞ​ንን በእ​ን​ቆ​ቅ​ልሽ ትፈ​ት​ነው ዘንድ መጣች።

2 በግ​መ​ሎ​ችም ላይ ሽቱና እጅግ ብዙ ወርቅ የከ​በ​ረም ዕንቍ አስ​ጭና ከታ​ላቅ ጓዝ ጋር ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ገባች፤ ወደ ሰሎ​ሞ​ንም በመ​ጣች ጊዜ በል​ብዋ ያለ​ውን ሁሉ ነገ​ረ​ችው።

3 ሰሎ​ሞ​ንም የጠ​የ​ቀ​ች​ውን ሁሉ ፈታ​ላት፤ ያል​ተ​ረ​ጐ​መ​ላ​ትና ከን​ጉሡ የተ​ሰ​ወረ ነገር አል​ነ​በ​ረም።

4 የሳ​ባም ንግ​ሥት የሰ​ሎ​ሞ​ንን ጥበብ ሁሉ፥ ሠር​ቶ​ትም የነ​በ​ረ​ውን ቤት፥

5 የሰ​ሎ​ሞ​ን​ንም የማ​ዕ​ዱን መብል፥ የብ​ላ​ቴ​ኖ​ቹ​ንም አቀ​ማ​መጥ፥ የሎ​ሌ​ዎ​ቹ​ንም ሥር​ዐት፥ አለ​ባ​በ​ሳ​ቸ​ው​ንም፥ ጠጅ አሳ​ላ​ፊ​ዎ​ቹ​ንም፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት የሚ​ያ​ቀ​ር​በ​ውን መሥ​ዋ​ዕት ባየች ጊዜ ተደ​ነ​ቀች።

6 ንጉ​ሡን ሰሎ​ሞ​ን​ንም አለ​ችው፥ “ስለ ነገ​ር​ህና ስለ ጥበ​ብህ በሀ​ገሬ ሳለሁ የሰ​ማ​ሁት ዝና እው​ነት ነው።

7 እኔም መጥቼ በዐ​ይኔ እስ​ካይ ድረስ የነ​ገ​ሩ​ኝን አላ​መ​ን​ሁም ነበር ፤ እነ​ሆም፥ እኩ​ሌ​ታ​ውን አል​ነ​ገ​ሩ​ኝም ነበር፤ በሀ​ገሬ ሳለሁ ከነ​ገ​ሩኝ ይልቅ የበ​ለጠ መል​ካም ተጨ​ማሪ አየሁ።

8 ሚስ​ቶ​ችህ የተ​መ​ሰ​ገኑ ናቸው፤ በፊ​ትህ ሁል​ጊዜ የሚ​ቆሙ፥ ጥበ​ብ​ህን የሚ​ሰሙ እነ​ዚህ አገ​ል​ጋ​ዮ​ች​ህም ምስ​ጉ​ኖች ናቸው።

9 አን​ተን በእ​ስ​ራ​ኤል ዙፋን ያስ​ቀ​ም​ጥህ ዘንድ የወ​ደደ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​መ​ሰ​ገነ ይሁን፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እስ​ራ​ኤ​ልን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ያጸ​ናው ዘንድ ወድ​ዶ​ታ​ልና ስለ​ዚህ በየ​ነ​ገ​ራ​ቸው ጽድ​ቅና ፍርድ ታደ​ርግ ዘንድ በላ​ያ​ቸው አነ​ገ​ሠህ።”

10 ለን​ጉ​ሡም መቶ ሃያ መክ​ሊት ወርቅ እጅ​ግም ብዙ ሽቶ፥ የከ​በ​ረም ዕንቍ ሰጠ​ችው፤ የሳባ ንግ​ሥት ለን​ጉሡ ለሰ​ሎ​ሞን እንደ ሰጠ​ችው ያለ የሽቶ ብዛት ከዚያ ወዲያ አል​መ​ጣም ነበር።

11 ከኦ​ፌ​ርም ወርቅ ያመ​ጣች የኪ​ራም መር​ከብ እጅግ ብዙ የተ​ጠ​ረበ እን​ጨ​ትና የከ​በረ ዕንቍ አመ​ጣች።

12 ንጉ​ሡም ከተ​ጠ​ረ​በው እን​ጨት ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤትና ለን​ጉሡ ቤት መከታ፥ ለመ​ዘ​ም​ራ​ኑም መሰ​ን​ቆና በገና አደ​ረገ፤ እስከ ዛሬም ድረስ በም​ድር ላይ እን​ደ​ዚያ ያለ የተ​ጠ​ረበ እን​ጨት ከቶ አል​መ​ጣም፤ በየ​ትም ቦታ አል​ታ​የም።

13 ንጉ​ሡም ሰሎ​ሞን በእጁ ከሰ​ጣት ሌላ፥ የወ​ደ​ደ​ች​ውን ሁሉ፥ ከእ​ር​ሱም የጠ​የ​ቀ​ች​ውን ሁሉ ለሳባ ንግ​ሥት ሰጣት፤ የከ​ለ​ከ​ላ​ትም የለም፤ እር​ስ​ዋም ተመ​ልሳ ከአ​ገ​ል​ጋ​ዮ​ችዋ ጋር ወደ ሀገ​ርዋ ሄደች።

14 በየ​ዓ​መቱ ለሰ​ሎ​ሞን የሚ​መ​ጣ​ለት የወ​ርቅ ሚዛን ስድ​ስት መቶ ስድሳ ስድ​ስት መክ​ሊት ወርቅ ነበረ።

15 ይኽ​ንም፥ ግብር የሚ​ያ​ስ​ገ​ብሩ ሰዎች፥ ነጋ​ዴ​ዎ​ችም፥ በዙ​ሪ​ያው ያሉ ነገ​ሥ​ታ​ትም ሁሉ፥ የም​ድ​ርም ሹሞች ከሚ​ያ​ወ​ጡት ሌላ ነው።

16 ንጉሡ ሰሎ​ሞ​ንም ከጥ​ፍ​ጥፍ ወርቅ ሁለት መቶ አላ​ባሽ አግሬ ጋሻ አሠራ፤ በአ​ን​ዱም አላ​ባሽ አግሬ ጋሻ ውስጥ የገ​ባው ወርቅ ሦስት መቶ ሰቅል ነበረ።

17 ከጥ​ፍ​ጥ​ፍም ወርቅ ሦስት መቶ ጋሻ አሠራ፤ በአ​ን​ዱም ጋሻ የገ​ባው ወርቅ ሦስት ምናን ነው፤ ንጉ​ሡም የሊ​ባ​ኖስ ዱር በተ​ባ​ለው ቤት ውስጥ አኖ​ራ​ቸው።

18 ንጉ​ሡም ደግሞ ከዝ​ሆን ጥርስ ታላቅ ዙፋን አሠራ፤ በጥ​ሩም ወርቅ ለበ​ጠው።

19 ወደ ዙፋ​ንም የሚ​ያ​ስ​ኬዱ ስድ​ስት እር​ከ​ኖች ነበሩ፤ በስ​ተ​ኋ​ላ​ውም ያለው የዙ​ፋኑ ራስ ክብ ነበረ፤ በላም ምስል የተ​ቀ​ረጸ በወ​ዲ​ህና በወ​ዲ​ያም መደ​ገ​ፊያ ነበ​ረው፤ በመ​ደ​ገ​ፊ​ያ​ዎ​ቹም አጠ​ገብ ሁለት አን​በ​ሶች ቆመው ነበር፤

20 በስ​ድ​ስ​ቱም እር​ከ​ኖች ላይ በዚ​ህና በዚያ ዐሥራ ሁለት አን​በ​ሶች ቆመው ነበር፤ በመ​ን​ግ​ሥ​ታት ሁሉ እን​ዲህ ያለ ሥራ አል​ተ​ሠ​ራም።

21 ንጉ​ሡም ሰሎ​ሞን ያሠ​ራው የመ​ጠጫ ዕቃ ሁሉ ወርቅ ነበረ፤ ኵስ​ኵ​ስ​ቱም የወ​ርቅ ነበረ፤ የሊ​ባ​ኖስ ዱር የተ​ባ​ለ​ውን የዚ​ያን ቤት ዕቃ ሁሉ በወ​ርቅ አስ​ለ​በ​ጠው። የብ​ርም ዕቃ አል​ነ​በ​ረም፤ በሰ​ሎ​ሞን ዘመን የብር ዋጋ ዝቅ​ተኛ ነበ​ርና።

22 ለን​ጉ​ሡም ከኪ​ራም መር​ከ​ቦች ጋር በባ​ሕር ውስጥ የተ​ር​ሴስ መር​ከ​ቦች ነበ​ሩት፤ በየ​ሦ​ስት ዓመ​ትም አንድ መር​ከብ ከተ​ር​ሴስ ወር​ቅና ብር፥ የተ​ቀ​ረ​ጸና የተ​ደ​ረ​ደረ ዕንቍ ይዞ ይመጣ ነበር።

23 ንጉ​ሡም ሰሎ​ሞን በብ​ል​ጥ​ግ​ናና በጥ​በብ ከም​ድር ነገ​ሥ​ታት ሁሉ እጅግ በልጦ ነበር።

24 የም​ድ​ርም ነገ​ሥት ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በልቡ ያኖ​ረ​ለ​ትን ጥበ​ቡን ይሰሙ ዘንድ የሰ​ሎ​ሞ​ንን ፊት ለማ​የት ይሹ ነበር።

25 እነ​ር​ሱም ሁሉ በዓ​መት በዓ​መቱ ገጸ በረ​ከ​ቱን፥ የብ​ርና የወ​ርቅ ዕቃ፥ ልብ​ስና የጦር መሣ​ሪያ፥ ሽቱም፥ ፈረ​ሶ​ችና በቅ​ሎ​ዎች እየ​ያዙ ይመጡ ነበር።

26 ሰሎ​ሞ​ንም ለሰ​ረ​ገ​ሎቹ ዐራት ሺህ እን​ስት ፈረ​ሶች ነበ​ሩት፤ ዐሥራ ሁለት ሺህ ፈረ​ሰ​ኞ​ችም ነበ​ሩት፤ በሰ​ረ​ገ​ሎ​ችም ከተ​ሞች ከን​ጉሡ ጋር በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም አኖ​ራ​ቸው። ሰሎ​ሞ​ንም ከወ​ንዙ ጀምሮ እስከ ፍል​ስ​ጥ​ኤም ምድ​ርና እስከ ግብፅ ድን​በር ድረስ በነ​ገ​ሥ​ታቱ ሁሉ ላይ ንጉሥ ነበር።

27 ንጉ​ሡም ብሩ​ንና ወር​ቁን በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም እንደ ድን​ጋይ እን​ዲ​በዛ አደ​ረ​ገው፤ የዝ​ግ​ባም እን​ጨት ብዛት በቆላ እን​ደ​ሚ​በ​ቅል ሾላ ሆነ።

28 ሰሎ​ሞ​ንም ፈረ​ሶ​ችን ከግ​ብ​ፅና ከቴ​ቁሄ ሀገር አስ​መጣ፤ የን​ጉ​ሡም ነጋ​ዴ​ዎች በገ​ን​ዘብ እየ​ገዙ ከቴ​ቁሄ ያመ​ጡ​አ​ቸው ነበር።

29 አን​ዱም ሰረ​ገላ በስ​ድ​ስት መቶ፥ አን​ዱም ፈረስ በመቶ ኀምሳ ብር ከግ​ብፅ ይወጣ ነበር። እን​ዲ​ሁም ለኬ​ጤ​ዎ​ና​ው​ያን ነገ​ሥ​ታ​ትና ለሶ​ርያ ነገ​ሥ​ታት ሁሉ በባ​ሕሩ በኩል ያወ​ጡ​ላ​ቸው ነበር።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos