Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -


ኢሳይያስ 21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


በባ​ቢ​ሎን፥ በኤ​ዶ​ም​ያ​ስና በዐ​ረ​ቢያ የተ​ነ​ገረ ትን​ቢት

1 ስለ ምድረ በዳ የተ​ነ​ገረ ቃል፤ ዐውሎ ነፋስ በም​ድረ በዳ እን​ደ​ሚ​ያ​ልፍ፥ እን​ዲሁ ከሚ​ያ​ስ​ፈራ ሀገር ከም​ድረ በዳ ይመ​ጣል።

2 ከባድ ራእይ ተነ​ገ​ረኝ፤ ወን​ጀ​ለ​ኛው ይወ​ነ​ጅ​ላል፤ በደ​ለ​ኛ​ውም ይበ​ድ​ላል። የኤ​ላም ሰዎ​ችና የሜ​ዶን መል​እ​ክ​ተኛ በእኔ ላይ ይመ​ጣሉ። ዛሬ ግን እጨ​ነ​ቃ​ለሁ፤ እረ​ጋ​ጋ​ለ​ሁም።

3 ስለ​ዚ​ህም ወገቤ ሕማም ተሞላ፤ እን​ደ​ም​ት​ወ​ልድ ሴትም ምጥ ያዘኝ፤ ከሕ​ማሜ የተ​ነሣ አል​ሰ​ማም፤ ከድ​ን​ጋ​ጤም የተ​ነሣ አላ​ይም።

4 ልቤ ሳተ፤ ኀጢ​አ​ቴም አሰ​ጠ​መኝ፤ ሰው​ነ​ቴም ደነ​ገ​ጠ​ብኝ።

5 ማዕ​ዱን አዘ​ጋጁ፤ ብሉ፤ ጠጡ፤ እና​ንተ አለ​ቆች ሆይ፥ ተነሡ፤ ጋሻ​ው​ንም አዘ​ጋጁ።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ብሎ​ኛ​ልና፥ “ፈጥ​ነህ ሂድ፤ ጕበ​ኛ​ንም አቁም፤ የሚ​ያ​የ​ው​ንም ይና​ገር፤ የሚ​ሰ​ማ​ው​ንም ያውራ።

7 ሁለት ፈረ​ሰ​ኞ​ችን ሲጋ​ልቡ አየሁ፤ አንዱ በአ​ህያ ላይ፥ ሁለ​ተ​ኛ​ውም በግ​መል ላይ ተቀ​ምጦ ነበር፤ ድም​ፃ​ቸው ግን እንደ ብዙ​ዎች ፈረ​ሰ​ኞች ድምፅ ነበረ።”

8 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጕበኛ ኦር​ያስ ተጠራ፤ እር​ሱም፥ “እነሆ እኔ አለሁ፤ መላ መዓ​ል​ቱ​ንና መላ ሌሊ​ቱን በማማ ላይ ቆሜ አለሁ።

9 እነ​ሆም፥ በፈ​ረ​ሶች የሚ​ቀ​መጡ፥ ሁለት ሁለት ሆነው የሚ​ሄዱ ፈረ​ሰ​ኞች ይመ​ጣሉ” ብሎ ጮኸ፤ እር​ሱም መልሶ፥ “ባቢ​ሎን ወደ​ቀች! ወደ​ቀች! ጣዖ​ቶ​ች​ዋም ሁሉ፥ የእ​ጆ​ች​ዋም ሥራ​ዎች ሁሉ በም​ድር ላይ ተጥ​ለው ደቀቁ” አለ።

10 እና​ንተ የተ​ረ​ፋ​ች​ሁና መከራ የም​ት​ቀ​በሉ ሆይ፥ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ የሠ​ራ​ዊት ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የነ​ገ​ረ​ኝ​ንና የሰ​ማ​ሁ​ትን ስሙ።

11 ስለ ኤዶ​ም​ያስ የተ​ነ​ገረ ነገር። አንዱ ከሴ​ይር፥ “ጕበኛ ሆይ፥ ሌሊቱ ምን ያህል ነው? ጕበኛ ሆይ፥ ሌሊቱ ምን ያህል ነው?” ብሎ ጠራኝ።

12 ጕበ​ኛ​ውም፥ “ይነ​ጋል፤ ደግ​ሞም ይመ​ሻል፤ ትጠ​ይቁ ዘንድ ብት​ወ​ድዱ ጠይቁ፤ ተመ​ል​ሳ​ች​ሁም ኑ፥” አለ።

13 ሌሊ​ትም በዲ​ዳ​ና​ው​ያን ጎዳና በዛ​ፎች ውስጥ ታድ​ራ​ለህ፤

14 በቴ​ማን የም​ት​ኖሩ ሆይ፥ ወደ ተጠ​ሙት ሰዎች ውኃ አምጡ፤

15 እን​ጀራ ይዛ​ችሁ ከሰ​ልፍ ከሸሹ ከብዙ ሰዎ​ችና በጦር ከጠፉ ከብዙ ሰዎች፥ ፍላጻ ከያዙ ከብዙ ሰዎ​ችና ጦር ከያዙ ከብዙ ሰዎች፥ ቀስ​ቶ​ቻ​ቸው ከተ​ሳ​ቡና በሰ​ልፍ ከወ​ደቁ ከብዙ ሰዎች ያመ​ለ​ጡ​ትን ተቀ​በ​ሏ​ቸው።

16 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ገና እን​ዲህ ብሎ​ኛ​ልና፥ “እንደ ምን​ደኛ ዓመት በአ​ንድ ዓመት ውስጥ የቄ​ዳር ልጆች ክብር ሁሉ ይጠ​ፋል፤

17 ከቀ​ስ​ተ​ኞች ቍጥር የቀ​ሩት፥ የቄ​ዳር ልጆች ኀያ​ላን፥ ያን​ሳሉ፤” የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይህን ተና​ግ​ሮ​አ​ልና።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos