የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

ማስታወቂያዎች

መላው መጽሐፍ ቅዱስ ብሉይ ኪዳን አዲስ ኪዳን


መጽሐፈ ሲራክ 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
መጽሐፈ ሲራክ 4

ለድ​ሆ​ችና ለች​ግ​ረ​ኞች መደ​ረግ ስለ​ሚ​ገ​ባው

1 ልጄ ሆይ፥ ድሃ​ውን የሚ​ኖ​ር​በ​ትን አት​ከ​ል​ክ​ለው፤ ከሚ​ለ​ም​ን​ህም ዐይ​ኖ​ች​ህን አት​መ​ልስ።

2 የተ​ራ​በች ሰው​ነ​ትን አታ​ሳ​ዝን፥ ያዘነ ሰው​ንም አታ​በ​ሳጭ።

3 ያዘነ ልቡ​ናን አታ​ስ​ደ​ን​ግጥ፤ የሚ​ለ​ም​ን​ህ​ንም አት​ለ​ፈው።

4 በሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ል​ህም ቤተ ሰብህ ላይ አት​ቈጣ፤ ከድ​ሃም ፊት​ህን አት​መ​ልስ።

5 ከሚ​ለ​ም​ን​ህም ዐይ​ን​ህን አት​መ​ልስ፤ ይረ​ግ​ም​ህም ዘንድ ለሰው ምክ​ን​ያት አት​ስ​ጠው፤

6 በል​ቡ​ናው አዝኖ ቢረ​ግ​ምህ ፈጣ​ሪው ጸሎ​ቱን ይሰ​ማ​ዋ​ልና።

7 በብዙ ሰዎች ዘንድ እን​ድ​ት​ወ​ደድ ሁን፤ በዳ​ኞች ዘንድ አገ​ል​ግል፤ ራስ​ህ​ንም ከፍ ከፍ አታ​ድ​ርግ።

8 ድሃ​ውን በጆ​ሮህ አድ​ም​ጠው፤ በየ​ዋ​ህ​ነ​ትም በጎ ቃልን መል​ስ​ለት።

9 የተ​በ​ደ​ለ​ው​ንም ሰው ከሚ​በ​ድ​ለው ሰው እጅ አድ​ነው፤ ለእ​ር​ሱም መፍ​ረ​ድን ቸል አት​በል።

10 አባቱ ለሞ​ተ​በት ልጅ እንደ አባት ሁነው፤ ለእ​ና​ቱም እንደ ባሏ ቁም​ላት፤ እንደ ልዑ​ልም ልጆች ትሆ​ና​ለህ፥ ከእ​ና​ት​ህም ይልቅ ይወ​ድ​ሃል።

ጥበብ ከፍ ከፍ እን​ደ​ም​ታ​ደ​ርግ

11 ጥበ​ብስ ልጆ​ች​ዋን ከፍ ከፍ አደ​ረ​ገ​ቻ​ቸው፤ የሚ​ፈ​ል​ጓ​ት​ንም ትቀ​በ​ላ​ቸ​ዋ​ለች።

12 እር​ሷን የወ​ደደ ሕይ​ወ​ቱን ወደደ፤ ወደ እር​ሷም የሚ​ገ​ሠ​ግሥ ሰው በደ​ስታ ይሞ​ላል።

13 አጥ​ንቶ የሚ​ይ​ዛት ሰውም ክብ​ርን ይወ​ር​ሳል፥ እር​ስ​ዋም ያደ​ረ​ች​በ​ትን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይባ​ር​ካል።

14 እር​ስ​ዋ​ንም የሚ​ያ​ገ​ለ​ግሉ ቅዱ​ሱን ያገ​ለ​ግ​ላሉ፤ የሚ​ወ​ዱ​ኣ​ት​ንም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይወ​ዳ​ቸ​ዋል።

15 እር​ስ​ዋን የሚ​ሰ​ማ​ትም አሕ​ዛ​ብን ይገ​ዛል፤ እር​ስ​ዋ​ንም የሚ​ያ​ደ​ም​ጣት ሰው ተዘ​ልሎ ይኖ​ራል።

16 ካመ​ን​ኻት ታገ​ኛ​ታ​ለህ፤ በዘ​መ​ን​ህም ከፍ ከፍ ታደ​ር​ግ​ሃ​ለች።

17 ከእ​ርሱ ጋር ትሄድ ዘንድ ትቀ​ድ​ማ​ለች፤ ፈጽ​ማም ታስ​ፈ​ራ​ዋ​ለች፥ ሰው​ነ​ቱን እስ​ክ​ታ​ስ​ገ​ዛና በተ​ግ​ሣ​ጽዋ እስ​ክ​ት​ፈ​ት​ነው ድረስ፥ ትገ​ር​ፈ​ዋ​ለች ታስ​ተ​ም​ረ​ዋ​ለ​ችም።

18 ከዚህ በኋላ ዳግ​መኛ ተቀ​ብላ ደስ ታሰ​ኘ​ዋ​ለች፤ ምሥ​ጢ​ር​ዋ​ንም ትገ​ል​ጥ​ለ​ታ​ለች።

19 ከእ​ርሷ ወጥቶ ቢስት ግን ትለ​የ​ዋ​ለች። በጠ​ላ​ቱም እጅ ትጥ​ለ​ዋ​ለች።

20 ጊዜ​ውን ጠብቅ፥ ከክፉ ነገ​ርም ተጠ​ን​ቀቅ፤ ስለ ነፍ​ስህ በማ​ፈር አታ​ድላ።

21 በማ​ፈር ኀጢ​አ​ትን የሚ​ሠራ አለና፤ በማ​ፈ​ርም ጽድ​ቅን የሚ​ሠራ ሞገ​ስ​ንም የሚ​ያ​ገኝ አለና።

22 ጕዳት በራ​ስህ ስለ​ሚ​ደ​ር​ስ​ብህ የሰው ፊት አይ​ተህ አታ​ድላ፥ ሰው​ነ​ት​ህን እን​ዳ​ት​ጥል አት​ፈር።

23 የሚ​ና​ገ​ርን ሰው መና​ገ​ሩን አት​ከ​ል​ክ​ለው፤ ከቃሉ የተ​ነሣ ጥበቡ ይታ​ወ​ቃ​ልና፥ ትም​ህ​ር​ቱም ከአ​ን​ደ​በቱ ንግ​ግር የተ​ነሣ ይታ​ወ​ቃ​ልና።

24 ጽድ​ቅን አት​ቃ​ወም። ስለ በደ​ል​ኸ​ውም በደል ንስሓ ግባ።

25 ኀጢ​አ​ት​ህ​ንም መና​ገር አት​ፈር፥ የውኃ ሙላ​ትን አት​ደ​ፋ​ፈር።

26 ለሰ​ነፍ ሰው ራስ​ህን አታ​ዋ​ርድ፤ ለታ​ላቅ ሰው ፊትም አታ​ድላ።

27 ፈጣ​ሪህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ አንተ ይከ​ራ​ከ​ር​ል​ሃ​ልና ለሞት እስ​ክ​ት​ደ​ርስ ስለ እው​ነት ተከ​ራ​ከር።

28 በአ​ፍህ አው​ታታ አት​ሁን፤ ሥራ​ህ​ንም ቸል አት​በል።

29 በቤ​ትህ እንደ አን​በሳ አስ​ፈሪ አት​ሁን፤ ቤተ ሰብ​ህ​ንም አታ​ስ​ደ​ን​ግጥ፤

30 ለመ​በ​ደር እጅ​ህን አት​ዘ​ርጋ። በመ​ክ​ፈ​ልም ጊዜ እጅ​ህን ለመ​ሰ​ብ​ሰብ አት​መ​ለስ።