Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የየ​ዕ​ለት የሕ​ይ​ወት መመ​ሪያ

1 ገን​ዘ​ብ​ህን በከ​ንቱ አት​በ​ትን፤ በቃ​ኝም አት​በል።

2 የሰ​ው​ነ​ት​ህን ፈቃድ አት​ከ​ተል።

3 እኔ ኀይ​ለኛ ነኝ፤ ማንስ ይች​ለ​ኛል አት​በል፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቀ​ልን ይበ​ቀ​ላ​ልና።

4 ኀጢ​አት ሠርቼ ፍዳ አል​ተ​ቀ​በ​ል​ሁም አት​በል፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብዙ ዘመን ይታ​ገ​ሣ​ልና።

5 ስለ ኀጢ​አ​ትህ ንስሓ መግ​ባ​ትን አት​ፍራ። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምሕ​ረቱ ብዙ ነው ኀጢ​አ​ቴ​ንም ይቅር ይለ​ኛል እያ​ልህ በኀ​ጢ​አት ላይ ኀጢ​አ​ትን አት​ጨ​ምር።

6 ምሕ​ረ​ትም መቅ​ሠ​ፍ​ትም ከእ​ርሱ ዘንድ ይመ​ጣ​ልና፤ መቅ​ሠ​ፍ​ቱም በኀ​ጢ​አ​ተኛ ሰው ላይ ይወ​ር​ዳል።

7 ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መገ​ዛ​ትን ቸል አት​በል። ሞት ድን​ገት ትመ​ጣ​ለ​ችና ከቀን ቀን አታ​ሳ​ልፍ፤ ፍዳህ ከመ​ቅ​ሠ​ፍት ጋራ በመ​ጣ​ብህ ጊዜ በመ​ከራ ትጨ​ነ​ቃ​ለህ።

8 በመ​ከ​ራህ ጊዜ አን​ተን ማዳን አይ​ች​ል​ምና፤ ለዐ​መፃ ገን​ዘብ አት​ሳሳ።


ራስን ስለ መግ​ዛ​ትና ግልጽ ስለ መሆን

9 ለሰው ሁሉ ምሥ​ጢ​ር​ህን አታ​ውጣ። የወ​ደ​ድ​ኸ​ው​ንም ሁሉ አት​ከ​ተል፤ ምላሱ ሁለት እንደ ሆነ ኀጢ​አ​ተኛ አት​ሁን።

10 አን​ተስ በጥ​በ​ብህ ጸን​ተህ ኑር፤ ቃል​ህም አንድ ይሁን።

11 ለመ​ስ​ማ​ትም ፈጣን ሁን፤ ቃልን ለመ​መ​ለስ ግን የዘ​ገ​የህ ሁን።

12 የም​ት​ነ​ግ​ረው ካለህ ለባ​ል​ን​ጀ​ራህ ንገ​ረው፤ ያለ​ዚያ ግን እጅ​ህን ባፍህ ላይ አድ​ርግ።

13 መከ​በ​ር​ህና መዋ​ረ​ድህ ከቃ​ልህ የተ​ነሣ ነው፤ የሰ​ውም ውድ​ቀቱ ከአ​ን​ደ​በቱ የተ​ነሣ ነው።

14 ሐሜ​ተኛ አት​ሁን፥ በአ​ን​ደ​በ​ት​ህም አው​ታታ አት​ሁን፤ የሌባ እፍ​ረቱ ጥቂት ነው። አን​ደ​በቱ ሁለት የሆነ ሰው ግን መከ​ራው ጽኑ ነው።

15 በታ​ላ​ቁም በታ​ና​ሹም ሰው ዘንድ ቸር ሆነህ ተገ​ለጥ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች