La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘኍል 33:2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ሙሴም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛዝ እንደ ተጓዙ የሰ​ፈ​ሩ​በ​ትን ጻፈ፥ እየ​ተ​ጓዙ ያደ​ሩ​በት ይህ ነው።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሙሴም በጕዟቸው ላይ ሳሉ የሰፈሩባቸውን ቦታዎች በእግዚአብሔር ትእዛዝ መዘገበ፤ በየቦታው እየሰፈሩ ያደረጉት ጕዞም ይህ ነው፦

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ሙሴም በጌታ ትእዛዝ የጉዞአቸው መነሻ የሆኑትን ስፍራዎቻቸውን ጻፈ፤ እንደ መነሻ ስፍራዎቻቸው ጉዞአቸው እንዲህ ነበረ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

በየጊዜው የሰፈሩባቸውን ቦታዎች ስሞች ሙሴ በእግዚአብሔር ትእዛዝ መሠረት ጻፈ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ሙሴም በእግዚአብሔር ትእዛዝ እንደ ጕዞአቸው አወጣጣቸውን ጻፈ፤ እንደ አወጣጣቸውም ጕዞአቸው እንዲህ ነበረ።

Ver Capítulo



ዘኍል 33:2
8 Referencias Cruzadas  

እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን፥ “የዐ​ማ​ሌ​ቅን ዝክር ከሰ​ማይ በታች ጨርሼ እደ​መ​ስ​ሳ​ለ​ሁና ይህን ለመ​ታ​ሰ​ቢያ በመ​ጽ​ሐፍ ጻፈው፤ በኢ​ያ​ሱም ጆሮ ተና​ገር” አለው።


በመ​ጀ​መ​ሪ​ያም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሙሴ ቃል እን​ዳ​ዘዘ ተጓዙ።


ሁለ​ተ​ኛ​ው​ንም በም​ል​ክቱ ስት​ነፉ በአ​ዜብ በኩል የሰ​ፈ​ሩት ይጓዙ፤ ሦስ​ተ​ኛ​ው​ንም በም​ል​ክቱ በነ​ፋ​ችሁ ጊዜ በባ​ሕር በኩል የሰ​ፈ​ሩት ይጓዙ፤ አራ​ተ​ኛ​ው​ንም በም​ል​ክቱ በነ​ፋ​ችሁ ጊዜ በመ​ስዕ በኩል የሰ​ፈ​ሩት ሠራ​ዊት ይጓዙ፤ ለማ​ስ​ጓዝ በም​ል​ክት ትነ​ፉ​ታ​ላ​ችሁ።


በሙ​ሴና በአ​ሮን እጅ ከሠ​ራ​ዊ​ቶ​ቻ​ቸው ጋር ከግ​ብፅ ከወጡ በኋላ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የሰ​ፈ​ሩ​በት ይህ ነው።


በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር ከመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ውም ወር በዐ​ሥራ አም​ስ​ተ​ኛው ቀን ከራ​ምሴ ተጓዙ፤ ከፋ​ሲካ በኋላ በነ​ጋው የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ከግ​ብ​ፃ​ው​ያን ሁሉ ፊት ከፍ ባለች እጅ ወጡ።


በሴ​ይር ተራራ መን​ገድ ከኮ​ሬብ እስከ ቃዴስ በርኔ ድረስ የዐ​ሥራ አንድ ቀን ጕዞ ነው።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፦ ‘ተነ​ሥ​ተህ በሕ​ዝቡ ፊት ተጓዝ፤ ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ልሰ​ጣ​ቸው ወደ ማል​ሁ​ላ​ቸው ምድር ይግቡ፤ ይው​ረ​ሱ​አ​ትም’ አለኝ።