ነህምያ 3:2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በአጠገቡም የኢያሪኮ ሰዎች ሠሩ፤ በአጠገባቸውም የአምሪ ልጅ የዘኩር ልጆች ሠሩ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ቀጥሎ ያለውንም የኢያሪኮ ሰዎች ሠሩ፤ እነርሱ ከሠሩት ቀጥሎ ደግሞ የአምሪ ልጅ ዛኩር ሠራ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በአጠገቡ የኢያሪኮ ሰዎች ሠሩ፤ በአጠገቡም የኢምሪ ልጅ ዛኩር ሠራ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የኢያሪኮ ሰዎች የዚያን ተከታይ ክፍል ሲሠሩ፥ ዘኩር የተባለው የኢምሪ ልጅ ከዚያ ቀጥሎ የሚገኘውን ክፍል ሠራ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በአጠገቡ የኢያሪኮ ሰዎች ሠሩ፥ በአጠገባቸውም የአምሪ ልጅ ዘኩር ሠራ። |
የአስናሃ ልጆችም የዓሣ በር ሠሩ፤ ሠረገሎቹንም አኖሩ፤ ሳንቃዎቹንም አቆሙ፥ ቍልፎቹንና መወርወሪያዎቹንም አደረጉ።