ዕዝራ 2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)ወደ ሀገራቸው የተመለሱ የአይሁድ ስም ዝርዝር ( ነህ. 7፥4-73 ) 1 የባቢሎንም ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን ከማረካቸው ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ፥ ወደ እየከተማቸው የተመለሱት የሀገር ልጆች እነዚህ ናቸው። 2 ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከሠራያ፥ ከሮሃልያ፥ ከመርዶክዮስ፥ ከበላሳን፥ ከመሴፋር፥ ከበጎዋይ፥ ከሬሁም፥ ከበዓና ጋር መጡ። የእስራኤልም ሕዝብ ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤ 3 የፋሮስ ልጆች ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት። 4 የሰፋጥያስ ልጆች ሦስት መቶ ሰባ ሁለት። 5 የኤራስ ልጆች ሰባት መቶ ሰባ አምስት። 6 ከያሱኤና ከዮአብ ልጆች የሆኑት የፈሐት ሞዓብ ልጆች ሁለት ሺህ ስምንት መቶ ዐሥራ ሁለት። 7 የኤላም ልጆች ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት። 8 የዛቱዕ ልጆች ዘጠኝ መቶ አርባ አምስት። 9 የዘካይ ልጆች ሰባት መቶ ስድሳ። 10 የባኒ ልጆች ስድስት መቶ አርባ ሁለት። 11 የቢባይ ልጆች ስድስት መቶ ሃያ ሦስት። 12 የዓዝጋድ ልጆች ሺህ ሁለት መቶ ሃያ ሁለት። 13 የአዶኒቃም ልጆች ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት። 14 የበጕዋይ ልጆች ሁለት ሺህ አምሳ ስድስት። 15 የዓዲን ልጆች አራት መቶ አምሳ አራት። 16 ከሕዝቅያስ ወገን የአጤር ልጆች ዘጠና ስምንት። 17 የቤሳይ ልጆች ሦስት መቶ ሃያ ሦስት። 18 የዮራ ልጆች መቶ ዐሥራ ሁለት። 19 የሐሱም ልጆች ሁለት መቶ ሃያ ሦስት። 20 የጋቤር ልጆች ዘጠና አምስት። 21 የቤተ ልሔም ልጆች መቶ ሃያ ሦስት። 22 የነጦፋ ልጆች አምሳ ስድስት። 23 የዓናቶት ልጆች መቶ ሃያ ስምንት። 24 የዓዝሞት ልጆች አርባ ሁለት። 25 የቂርያትይዓሪምና የቃፌር፥ የብኤሮትም ልጆች ሰባት መቶ አርባ ሦስት። 26 የራማና የጋባዕ ልጆች ስድስት መቶ ሃያ አንድ። 27 የመኪማስ ሰዎች መቶ ሃያ ሁለት። 28 የቤቴልና የጋይ ሰዎች ሁለት መቶ ሃያ ሦስት። 29 የናባው ልጆች አምሳ ሁለት። 30 የመጌባስ ልጆች መቶ አምሳ ስድስት። 31 የኤላማር ልጆች ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት። 32 የኤላም ልጆች ሦስት መቶ ሃያ። 33 የሎድ፥ የሐዲድና የኦኖም ልጆች ሰባት መቶ ሃያ አምስት። 34 የኢያሪኮ ልጆች ሦስት መቶ አርባ አምስት። 35 የሴዓናህ ልጆች ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ሠላሳ። 36 ካህናቱ ከኢያሱ ወገን የዮዳኤ ልጆች ዘጠኝ መቶ ሰባ ሦስት። 37 የኢሜር ልጆች ሺህ አምሳ ሁለት። 38 የፋስኮር ልጆች ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት። 39 የኤረም ልጆች ሺህ ዐሥራ ሰባት። 40 ሌዋውያኑ፤ ከሁድያ ልጆች ወገን የኢዮስስና የቀዳምሔል ልጆች ሰባ አራት። 41 መዘምራኑ የአሳፍ ልጆች መቶ ሃያ ስምንት። 42 የበረኞች ልጆች፥ የሰሎም ልጆች፥ የአጤር ልጆች፥ የጤልሞን ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የሐጢጣ ልጆች፥ የሰበዋይ ልጆች ሁሉ መቶ ሠላሳ ዘጠኝ። 43 ናታኒም፤ የሲሓ ልጆች፥ የሐሡፊ ልጆች፥ የጠብዖት ልጆች፤ 44 የቃዴስ ልጆች፥ የሲሔል ልጆች፥ የፋዶን ልጆች፤ 45 የልባና ልጆች፥ የአጋባ ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ 46 የአጋብ ልጆች፥ የሰላሚ ልጆች፥ የሐናን ልጆች፤ 47 የጋዱል ልጆች፥ የጋሐር ልጆች፥ የራእያ ልጆች፤ 48 የረአሶን ልጆች፥ የኒቆዳ ልጆች፥ የጋሴም ልጆች፤ 49 የዓዝያት ልጆች፥ የፋሒስ ልጆች፥ የባሲ ልጆች፤ 50 የአሲና ልጆች፥ የምዑናውያን ልጆች፥ የናፌሶን ልጆች፤ 51 የበቅቡቅ ልጆች፥ የሐቁፋ ልጆች፥ የሐርሑር ልጆች፤ 52 የበስሎት ልጆች፥ የማሁድ ልጆች፥ የአሪስ ልጆች፤ 53 የበርቆስ ልጆች፥ የሲሣራ ልጆች፥ የቴማ ልጆች፥ 54 የንስያ ልጆች፥ የአጡፋ ልጆች። 55 የሰሎሞን አገልጋዮች ልጆች፤ የሳጢ ልጆች፥ የሰፌርታ ልጆች፥ የፋዱርሓ ልጆች፤ 56 የኢያሔል ልጆች፥ የደርቆን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፤ 57 የሰፋጥያስ ልጆች፥ የአጤል ልጆች፥ የፎኬርት ልጆች፥ የሐፂባይም ልጆች፥ የአሚ ልጆች። 58 እነዚህ ናታኒም ሁሉና የሰሎሞን አገልጋዮች ልጆች ሦስት መቶ ዘጠና ሁለት ነበሩ። 59 ከቲልሜላ፥ ከቴላርሳ፥ ከክሩብ፥ ከሐዳን፥ ከኤሜር የወጡ እነዚህ ነበሩ፤ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ወይም ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም፤ 60 የዳላያ ልጆች፥ የጦብያ ልጆች፥ የኒቆዳ ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ ሁለት ነበሩ። 61 ከካህናቱም ልጆች፤ የአብያ ልጆች፥ የአቆስ ልጆች፥ ከገለዓዳዊው ከቤርዜሊ ልጆች ሚስት ያገባ፥ በስማቸውም የተጠራ የቤርዜሊ ልጆች። 62 እነዚህ በትውልድ መጽሐፍ ትውልዳቸውን ፈለጉ፤ ነገር ግን አልተገኘም፤ ከክህነትም ተከለከሉ። 63 ሐቲርሰስታም፥ “በኡሪምና በቱሚም የሚፈርድ ካህን እስኪነሣ ድረስ ከቅዱሰ ቅዱሳኑ አትበሉም” አላቸው። 64 ጉባኤው ሁሉ አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስድሳ ነበሩ። 65 ይኸውም ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ሠላሳ ሰባት ከነበሩ ከሎሌዎቻቸውና ከገረዶቻቸው ሌላ ሁለት መቶ ወንዶች መዘምራንና ሴቶች መዘምራትም ነበሩአቸው። 66 ፈረሶቻቸውም ሰባት መቶ ሠላሳ ስድስት፥ በቅሎዎቻቸውም ሁለት መቶ አርባ አምስት፥ 67 ግመሎቻቸውም አራት መቶ ሠላሳ አምስት፥ አህዮቻቸውም ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ነበሩ። 68 በኢየሩሳሌምም ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤት በመጡ ጊዜ ከአባቶች ቤቶች አለቆች አያሌዎች ለእግዚአብሔር ቤት በስፍራው ይሠሩት ዘንድ በፈቃዳቸው ሰጡ። 69 ስድሳ አንድ ሺህም የወርቅ ዳሪክ፥ አምስት ሺህም ምናን ብር፥ አንድ መቶም የካህናት ልብስ እንደ ችሎታቸው ወደ ሥራው ቤተ መዛግብት አቀረቡ። 70 ካህናቱና ሌዋውያኑም፥ ከሕዝቡም አያሌዎች፥ መዘምራኑና በረኞቹም፥ ናታኒምም በከተሞቻቸው፥ እስራኤልም ሁሉ በከተሞቻቸው ተቀመጡ። |