La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘሌዋውያን 8:3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ማኅ​በ​ሩ​ንም ሁሉ ወደ ምስ​ክሩ ድን​ኳን ደጃፍ ሰብ​ስ​ባ​ቸው።”

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ማኅበሩን በሙሉ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ሰብስብ።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ማኅበሩንም ሁሉ ወደ መገናኛው ድንኳን ደጃፍ ሰብስብ።”

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ከዚያም የእስራኤልን ሕዝብ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ሰብስብ።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ማኅበሩንም ሁሉ ወደ መገናኛው ድንኳን ደጃፍ ሰብስባቸው።

Ver Capítulo



ዘሌዋውያን 8:3
16 Referencias Cruzadas  

የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ታቦት ከቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪም ያመጡ ዘንድ ዳዊት እስ​ራ​ኤ​ልን ሁሉ ከግ​ብፅ ዳርቻ ጀምሮ እስከ ኤማት መግ​ቢያ ድረስ ሰበ​ሰበ።


ዳዊ​ትም ወዳ​ዘ​ጋ​ጀ​ላት ስፍራ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት ያመጣ ዘንድ እስ​ራ​ኤ​ልን ሁሉ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሰበ​ሰበ።


በሁ​ለ​ተ​ኛ​ውም ወር የቂ​ጣ​ውን በዓል ያደ​ርጉ ዘንድ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ብዙ ሕዝብ ተሰ​በ​ሰቡ፤ እጅ​ግም ታላቅ ጉባኤ ነበረ።


ንጉ​ሡና አለ​ቆቹ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ያለ የእ​ስ​ራ​ኤል ጉባኤ ሁሉ በሁ​ለ​ተ​ኛው ወር ፋሲ​ካ​ውን ያደ​ርጉ ዘንድ ተማ​ከሩ።


የይ​ሁ​ዳም ጉባኤ ሁሉ ፥ ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያኑ፥ ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም የመጡ ጉባኤ ሁሉ፥ ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሀገር የመ​ጡ​ትና በይ​ሁዳ የኖ​ሩት እን​ግ​ዶች ደስ አላ​ቸው።


በዚያ ጊዜም ሰሎ​ሞን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ኪዳን ታቦት ከዳ​ዊት ከተማ ከጽ​ዮን ያወጡ ዘንድ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችና የነ​ገድ አለ​ቆ​ችን ሁሉ፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ልጆች አባ​ቶች ቤቶች መሳ​ፍ​ንት ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሰበ​ሰበ።


ንጉ​ሡም ሰሎ​ሞ​ንና የእ​ስ​ራ​ኤል ማኅ​በር ሁሉ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈሩ ሁሉ በአ​ን​ድ​ነት በታ​ቦቷ ፊት ሆነው ከብ​ዛት የተ​ነሣ የማ​ይ​ቈ​ጠ​ሩ​ት​ንና የማ​ይ​መ​ጠ​ኑ​ትን በጎ​ችና በሬ​ዎች ይሠዉ ነበር።


ሰባ​ተ​ኛ​ውም ወር በደ​ረሰ ጊዜ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች በከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው ነበሩ። ሕዝ​ቡም ሁሉ በው​ኃው በር ፊት ወዳ​ለው አደ​ባ​ባይ እንደ አንድ ሰው ሆነው ተሰ​በ​ሰቡ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለእ​ስ​ራ​ኤል ያዘ​ዘ​ውን የሙ​ሴን ሕግ መጽ​ሐፍ ያመጣ ዘንድ ጸሓ​ፊ​ውን ዕዝ​ራን ነገ​ሩት።


የሚ​ያ​ነ​ጻ​ውም ካህን እነ​ዚ​ህን ነገ​ሮች፥ የሚ​ነ​ጻ​ው​ንም ሰው በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ደጃፍ አጠ​ገብ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ያቀ​ር​ባ​ቸ​ዋል።


“አሮ​ንን፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ልጆ​ቹን፥ ልብ​ሱ​ንም፥ የቅ​ብ​ዐ​ቱ​ንም ዘይት፥ ለኀ​ጢ​አት መሥ​ዋ​ዕ​ትም የሆ​ነ​ውን ወይ​ፈን፥ ሁለ​ቱ​ንም አውራ በጎች፥ የቂ​ጣ​ው​ንም እን​ጀራ መሶብ ውሰድ፤


ሙሴም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ዘ​ዘው አደ​ረገ፤ ማኅ​በ​ሩ​ንም ሁሉ ወደ ምስ​ክሩ ድን​ኳን ደጃፍ ሰበ​ሰበ።


“ይህ​ችን በት​ር​ህን ውሰድ፤ አን​ተና ወን​ድ​ምህ አሮ​ንም ማኅ​በ​ሩን ሰብ​ስቡ፤ ዐለ​ቷ​ንም በፊ​ታ​ቸው እዘ​ዟት፤ ውኃ ትሰ​ጣ​ለች፤ ከድ​ን​ጋ​ይ​ዋም ውኃ ታወ​ጡ​ላ​ቸ​ዋ​ላ​ችሁ፤ እን​ዲ​ሁም ማኅ​በ​ሩን፥ ከብ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ታጠ​ጡ​ላ​ቸ​ዋ​ላ​ችሁ።”


ከዚ​ያም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሙሴን፥ “ሕዝ​ቡን ሰብ​ስብ፤ የሚ​ጠ​ጡት ውኃ እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ” ብሎ ወደ ተና​ገ​ረ​ላት ጕድ​ጓድ ሄዱ።


ሌዋ​ው​ያ​ን​ንም በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ፊት አቅ​ርብ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ልጆች ማኅ​በር ሁሉ ሰብ​ስብ።


ኀም​ሳው ቀንም በተ​ፈ​ጸመ ጊዜ፥ ሁሉም በአ​ን​ድ​ነት በአ​ንድ ቦታ ተሰ​ብ​ስ​በው ነበር።