La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘሌዋውያን 25:9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ከዚ​ያም በኋላ በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር ከወሩ በዐ​ሥ​ረ​ኛው ቀን በም​ድ​ራ​ችሁ ሁሉ በቀ​ንደ መለ​ከት ታው​ጃ​ለህ፤ በማ​ስ​ተ​ስ​ረያ ቀን በም​ድ​ራ​ችሁ ሁሉ በቀ​ንደ መለ​ከት ታው​ጃ​ላ​ችሁ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ከዚያም በኋላ በሰባተኛው ወር በዐሥረኛው ቀን፣ መለከት ይነፋ፤ በማስተስረያ ቀንም በምድራችሁ ሁሉ መለከት ንፉ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ከዚያም በኋላ በሰባተኛው ወር በአሥረኛው ቀን የቀንደ መለከትን ድምፅ ከፍ አድርገህ ታሰማለህ፤ በማስተስረያ ቀን በምድራችሁ ሁሉ የቀንደ መለከትን ድምፅ ታሰማላችሁ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ሰባተኛው ወር በገባ በዐሥረኛው ቀን በሚውለው የኃጢአት ስርየት ቀን በመላይቱ ምድር የእምቢልታ ድምፅ የሚያሰማ ሰው ትልካለህ፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ከዚያም በኋላ በሰባተኛው ወር በአሥረኛው ቀን በቀንደ መለከት ታውጃለህ፤ በማስተስረያ ቀን በምድራችሁ ሁሉ በቀንደ መለከት ታውጃላችሁ።

Ver Capítulo



ዘሌዋውያን 25:9
20 Referencias Cruzadas  

መከ​ራን ባሳ​የ​ኸን ዘመን ፋንታ፥ ክፉ​ንም ባየ​ን​ባት ዘመን ፋንታ ደስ ይለ​ናል።


ባሪ​ያ​ዎ​ች​ህ​ንና ሥራ​ህን እይ፥ ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ምራ​ቸው።


በዚ​ያም ቀን እን​ዲህ ይሆ​ናል፤ ታላቅ መለ​ከት ይነ​ፋል፤ በአ​ሦ​ርም የጠፉ፥ በግ​ብፅ ምድ​ርም የተ​ሰ​ደዱ ይመ​ጣሉ፤ በተ​ቀ​ደ​ሰ​ውም ተራራ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይሰ​ግ​ዳሉ።


“ስለ​መ​ቅ​ደሱ፥ስለ ምስ​ክ​ሩም ድን​ኳን፥ ስለ መሠ​ዊ​ያ​ውም ማስ​ተ​ስ​ረ​ያና ስለ ካህ​ና​ትም ማን​ጻት ከፈ​ጸመ በኋላ ደኅ​ነ​ኛ​ውን ፍየል ያቀ​ር​ባል።


“ይህም የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ይሁ​ን​ላ​ችሁ።


በዚህ ቀን ትነጹ ዘንድ ማስ​ተ​ስ​ረያ ይሆ​ን​ላ​ች​ኋ​ልና በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር ከወ​ሩም በዐ​ሥ​ረ​ኛው ቀን ራሳ​ች​ሁን አስ​ጨ​ን​ቋት፤ የሀ​ገር ልጅም፥ በእ​ና​ን​ተም መካ​ከል የተ​ቀ​መጠ እን​ግዳ ሥራን ሁሉ አት​ሥ​ሩ​በት፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ከኀ​ጢ​አ​ታ​ችሁ ሁሉ ትነ​ጻ​ላ​ችሁ።


“ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እን​ዲህ ብለህ ንገ​ራ​ቸው፦ በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር ከወ​ሩም በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ቀን ዕረ​ፍት፥ በመ​ለ​ከት ድምፅ መታ​ሰ​ቢያ፥ የተ​ቀ​ደ​ሰች ጉባኤ ትሁ​ን​ላ​ችሁ።


“በዚህ በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር ዐሥ​ረ​ኛዋ ቀን የማ​ስ​ተ​ስ​ረያ ቀን ናት፤ ቅድ​ስት ጉባኤ ትሁ​ን​ላ​ችሁ፤ ሰው​ነ​ታ​ች​ሁን አስ​ጨ​ን​ቋት፤ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት አቅ​ርቡ።


“የዓ​መ​ታ​ትን ሰባት ሰን​በ​ቶች ሰባት ጊዜ ሰባት ለራ​ስህ ትቈ​ጥ​ራ​ለህ፤ እነ​ዚ​ህም ሰባት የዓ​መ​ታት ሱባ​ዔ​ያት አርባ ዘጠኝ ዓመ​ታት ይሆ​ናሉ።


እር​ሻ​ው​ንም ከኢ​ዮ​ቤ​ልዩ ዓመት ጀምሮ ቢሳል፥ እንደ ግምቱ መጠን ይቆ​ማል።


በኢ​ዮ​ቤ​ልዩ ዓመት እር​ሻው የም​ድ​ሪቱ ባለ ርስት ወደ ነበ​ረው ወደ ሸጠው ሰው ይመ​ለ​ሳል፤ የራሱ ወሰን ምድር ነውና።


ደግሞ በደ​ስ​ታ​ችሁ ቀን፥ በበ​ዓ​ላ​ታ​ች​ሁም ዘመን፥ በወ​ርም መባቻ፥ በሚ​ቃ​ጠ​ልም መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ች​ሁና በደ​ኅ​ን​ነት መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ችሁ ላይ መለ​ከ​ቶ​ችን ንፉ፤ እነ​ር​ሱም በአ​ም​ላ​ካ​ችሁ ፊት ለመ​ታ​ሰ​ቢያ ይሆ​ኑ​ላ​ች​ኋል፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝና።”


ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ኢዮ​ቤ​ልዩ በሆነ ጊዜ ርስ​ታ​ቸው ሴቶቹ ወደ አገ​ቡ​በት ወደ ሌላ ነገድ ርስት ይጨ​መ​ራል፤ እነሆ፥ ርስ​ታ​ቸው ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን ነገድ ርስት ይጐ​ድ​ላል።”


ነገር ግን እን​ዲህ እላ​ለሁ፤ በውኑ እስ​ራ​ኤል ብቻ አል​ሰ​ሙ​ምን? መጽ​ሐፍ “ነገ​ራ​ቸው በም​ድር ሁሉ ተሰማ፤ ቃላ​ቸ​ውም እስከ ዓለም ዳርቻ ደረሰ” ብሎ የለ​ምን?


በኀ​ይ​ልና በተ​አ​ም​ራት፥ በመ​ን​ፈስ ቅዱስ ኀይ​ልና ድንቅ ሥራን በመ​ሥ​ራ​ትም፥ ከኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም አው​ራ​ጃ​ዎች ጀምሬ እስከ እል​ዋ​ሪ​ቆን ድረስ እንደ አስ​ተ​ማ​ርሁ፥ የክ​ር​ስ​ቶ​ስ​ንም ወን​ጌል ፈጽሞ እንደ ሰበ​ክሁ እና​ገር ዘንድ እደ​ፍ​ራ​ለሁ።


ከእናንተ ወጥቶ የጌታ ቃል በመቄዶንያና በአካይያ ብቻ አልተሰማምና፤ ነገር ግን ምንም እንድንናገር እስከማያስፈልግ ድረስ፥ በእግዚአብሔር ዘንድ የሚሆን እምነታችሁ በሁሉ ስፍራ ተወርቶአል።


ሰባ​ትም ካህ​ናት ሰባት ቀንደ መለ​ከት በታ​ቦቱ ፊት ይያዙ፤ በሰ​ባ​ተ​ኛ​ውም ቀን ከተ​ማ​ዪ​ቱን ሰባት ጊዜ ዙሩ፤ ካህ​ና​ቱም ቀንደ መለ​ከ​ቱን ይንፉ።