ሉቃስ 23:21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) እነርሱ ግን፥ “ስቀለው! ስቀለው!” እያሉ ይጮሁ ነበር። አዲሱ መደበኛ ትርጒም እነርሱ ግን፣ “ስቀለው! ስቀለው!” እያሉ ይጮኹ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ነገር ግን እነርሱ “ስቀለው! ስቀለው!” እያሉ ይጮኹ ነበር። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሕዝቡ ግን “ስቀለው! ስቀለው!” እያለ ጮኸ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ነገር ግን እነርሱ፦ ስቀለው ስቀለው እያሉ ይጮኹ ነበር። |
ጲላጦስም ለሦስተኛ ጊዜ፥ “ምን ክፉ ነገር አደረገ? እነሆ፥ ለሞት የሚያበቃ ምክንያት አላገኘሁበትም፤ እንኪያስ ልግረፈውና ልተወው” አላቸው።
እነርሱ ግን፥ “አስወግደው! ስቀለው!” እያሉ ጮሁ። ጲላጦስም፥ “ንጉሣችሁን ልስቀለውን?” አላቸው፤ ሊቃነ ካህናቱም፥ “ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ የለንም” ብለው መለሱ።