ሰቈቃወ 5:15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የልባችን ደስታ ተሽሮአል፤ ዘፈናችን ወደ ልቅሶ ተለውጦአል። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ደስታ ከልባችን ጠፍቷል፤ ጭፈራችን ወደ ልቅሶ ተለውጧል። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የልባችን ደስታ ቀርቶአል፥ ዘፈናችን ወደ ልቅሶ ተለውጦአል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ደስታ ከልባችን ጠፍቶአል፤ በጭፈራችን ቦታ ሐዘን ተተክቶአል። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የልባችን ደስታ ቀርቶአል፥ ዘፈናችን ወደ ልቅሶ ተለውጦአል። |
ከእነርሱም የሐሤትን ድምፅና የደስታን ድምፅ፥ የወንድ ሙሽራን ድምጽና የሴት ሙሽራን ድምፅ፥ የወፍጮንም ድምፅ የመብራትንም ብርሃን አስቀራለሁ።
ዓመት በዓላችሁንም ወደ ልቅሶ፥ ዝማሬያችሁንም ወደ ዋይታ እለውጣለሁ፤ ማቅንም በወገብ ሁሉ ላይ፥ ቡሃነትንም በራስ ሁሉ ላይ ላይ አመጣለሁ፤ እንደ ወዳጅ ልቅሶ አደርጋችኋለሁ፤ ከእርሱም ጋር ያሉት እንደ መከራ ቀን ይሆናሉ።