ኢዮብ 41:14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የአካሉ ሥጋም የተነባበረ ነው፤ ጎጂ ነገርን ቢያፈስሱበትም አይንቀሳቀስም፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም አስፈሪ ጥርሶቹ የተገጠገጡበትን፣ የአፉን ደጅ ማን ደፍሮ ይከፍታል? መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) አንገቱ በጣም ጠንካራ ነው፥ ግርማ በፊቱ ይዘፍናል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም እጅግ የሚያስፈሩ ጥርሶች ያሉበት አፉን ከፍቶ መንጋጋውን ሊያላቅቀው የሚችል ማን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በአንገቱ ኃይል ታድራለች፥ ግርማ በፊቱ ይዘፍናል። |
በአደባባይም ደጆቹ በሚዘጉበት ቀን፥ የወፍጮ ድምፅ ሲላሽ፥ ከዎፍ ድምፅ የተነሣ ሰው ሲነሣ፥ ዜማም የሚጮኹ ሴቶች ልጆች ሁሉ ዝግ ሲሉ፤