Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 58 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ አታ​ጥፋ። ሳኦል ይገ​ድ​ሉት ዘንድ ቤቱን እን​ዲ​ጠ​ብቁ በላከ ጊዜ የዳ​ዊት ቅኔ።

1 አም​ላኬ ሆይ፥ ከጠ​ላ​ቶች አድ​ነኝ፤ በላ​ዬም ከቆ​ሙት አስ​ጥ​ለኝ።

2 ከዐ​መፅ አድ​ራ​ጊ​ዎች ታደ​ገኝ፥ ከደም ሰዎ​ችም አድ​ነኝ።

3 እነሆ፥ ነፍ​ሴን አድ​ድ​ነ​ዋ​ታ​ልና፥ ብር​ቱ​ዎ​ችም በላዬ ተነሡ፤ አቤቱ፥ በበ​ደ​ሌም አይ​ደ​ለም፥ በኀ​ጢ​አ​ቴም አይ​ደ​ለም።

4 ያለ በደል ሮጥሁ ተዘ​ጋ​ጀ​ሁም፤ ተነሥ፥ ተቀ​በ​ለኝ፥ እይም።

5 አን​ተም አቤቱ፥ የኀ​ያ​ላን አም​ላክ፥ የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ፥ አሕ​ዛ​ብን ሁሉ ጐብ​ኛ​ቸው፥ ይቅ​ርም በላ​ቸው፤ ዐመፅ የሚ​ያ​ደ​ር​ጉ​ትን ሁሉ ግን አት​ማ​ራ​ቸው።

6 ማታ ይመ​ለሱ እንደ ውሾ​ችም ይራቡ፥ በከ​ተ​ማም ይዙሩ።

7 እነሆ፥ በአ​ፋ​ቸው ይና​ገ​ራሉ፤ ሰይ​ፍም በከ​ን​ፈ​ሮ​ቻ​ቸው አለ፤

8 የም​ት​ሰ​ማ​ቸው አንተ ግን አቤቱ፥ ትሥ​ቅ​ባ​ቸ​ዋ​ለህ፥ አሕ​ዛ​ቡ​ንም ሁሉ ትን​ቃ​ቸ​ዋ​ለህ፥

9 ኀይ​ሌን ወደ አንተ አስ​ጠ​ጋ​ለሁ፥ አንተ አም​ላ​ኬና መጠ​ጊ​ያዬ ነህና።

10 የአ​ም​ላኬ ይቅ​ር​ታው ይድ​ረ​ሰኝ አም​ላኬ በጠ​ላ​ቶቼ ላይ አሳ​የኝ።

11 ሕግ​ህን እን​ዳ​ይ​ረሱ አት​ግ​ደ​ላ​ቸው፤ አቤቱ፥ አም​ላ​ኬና ረዳቴ፥ በኀ​ይ​ልህ በት​ና​ቸው፥ አዋ​ር​ዳ​ቸ​ውም።

12 ስለ አፋ​ቸው ኀጢ​አት ስለ ከን​ፈ​ራ​ቸ​ውም ቃል፥ በት​ዕ​ቢ​ታ​ቸው ይጠ​መዱ ከመ​ር​ገ​ማ​ቸ​ውና ከሐ​ሰ​ታ​ቸው የተ​ነሣ፥ ፍጻ​ሜ​ያ​ቸው ይታ​ወ​ቃል።

13 ኋላ በሚ​መጣ መቅ​ሠ​ፍት ያል​ቃሉ፤ የያ​ዕ​ቆ​ብም አም​ላክ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ እን​ዲ​ገዛ ይወቁ።

14 ማታ ይመ​ለሱ እንደ ውሾ​ችም ይራቡ፥ በከ​ተ​ማም ይዙሩ።

15 እነ​ር​ሱም መብል ለመ​ፈ​ለግ ይበ​ተኑ፤ የጠ​ገቡ እንደ ሆነም ያን​ጐ​ራ​ጕ​ራሉ።

16 እኔ ግን ለኀ​ይ​ልህ እቀ​ኛ​ለሁ፤ በም​ሕ​ረ​ት​ህም በማ​ለዳ ደስ ይለ​ኛል፤ በመ​ከ​ራዬ ቀን መጠ​ጊ​ያ​ዬና አም​ባዬ ሆነ​ኽ​ል​ኛ​ልና።

17 አንተ ረዳቴ ነህ፥ ለአ​ን​ተም ለአ​ም​ላኬ እዘ​ም​ራ​ለሁ፤ አንተ፥ አም​ላኬ፥ መጠ​ጊ​ያዬ ነህና አም​ላ​ኪዬ ምሕ​ረ​ቴም ነህና።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos