La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኤርምያስ 8:1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

“በዚ​ያም ዘመን ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ የይ​ሁዳ ነገ​ሥ​ታ​ትን አጥ​ን​ትና የመ​ኳ​ን​ን​ቱን አጥ​ንት፥ የካ​ህ​ና​ቱን አጥ​ን​ትና የነ​ቢ​ያ​ቱን አጥ​ንት፥ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም ሰዎች አጥ​ንት ከመ​ቃ​ብ​ሮ​ቻ​ቸው ያወ​ጣሉ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

“ ‘በዚያ ጊዜ፣ ይላል እግዚአብሔር፤ የይሁዳ ነገሥታትና መኳንንት ዐፅም፣ የካህናትና የነቢያት ዐፅም፣ የኢየሩሳሌም ሕዝብ ዐፅም ከየመቃብራቸው ይወጣል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

“በዚያን ዘመን፥ ይላል ጌታ፥ የይሁዳን ነገሥታት አጥንትና የመኳንንቶቿን አጥንት፥ የካህናቱን አጥንትና የነቢያቱን አጥንት፥ የኢየሩሳሌምንም ሰዎች አጥንት ከመቃብራቸው ያወጣሉ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

“በዚያን ጊዜ የይሁዳ ነገሥታትና የመኳንንት ዐፅሞች እንዲሁም የካህናቱና የነቢያቱ የሌላውም የኢየሩሳሌም ነዋሪ ሕዝብ ዐፅሞች ሁሉ ከየመቃብሩ ተለቅመው ይወጣሉ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

በዚያን ዘመን፥ ይላል እግዚአብሔር፥ የይሁዳን ነገሥታት አጥንትና የመኳንንቶቹን አጥንት፥ የካህናቱን አጥንትና የነቢያቱን አጥንት፥ የኢየሩሳሌምንም ሰዎች አጥንት ከመቃብራቸው ያወጣሉ።

Ver Capítulo



ኤርምያስ 8:1
12 Referencias Cruzadas  

የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰው በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ፥ “መሠ​ዊያ ሆይ፥ መሠ​ዊያ ሆይ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ እነሆ፥ ስሙ ኢዮ​ስ​ያስ የሚ​ባል ልጅ ለዳ​ዊት ቤት ይወ​ለ​ዳል፤ ዕጣ​ንም የሚ​ያ​ጥ​ኑ​ብ​ህን የኮ​ረ​ብታ መስ​ገ​ጃ​ዎ​ቹን ካህ​ናት ይሠ​ዋ​ብ​ሃል፤ የሰ​ዎ​ቹ​ንም አጥ​ንት ያቃ​ጥ​ል​ብ​ሃል” ብሎ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ጠራ።


ኢዮ​ስ​ያ​ስም ዘወር ብሎ በከ​ተ​ማው የነ​በ​ሩ​ትን መቃ​ብ​ሮች አየ፤ ኢዮ​ር​ብ​ዓ​ምም በበ​ዓል ጊዜ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው እንደ ተና​ገ​ረው እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል፥ ልኮ ከመ​ቃ​ብ​ሮቹ አጥ​ን​ቶ​ቹን አስ​ወጣ፥ በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይም አቃ​ጠ​ላ​ቸው፥ አረ​ከ​ሰ​ውም። ዘወ​ርም ብሎ ይህን ቃል ወደ ተና​ገ​ረው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው መቃ​ብር ዐይ​ኖ​ቹን አቀና። እን​ዲ​ህም አለ፦


በዚ​ያም የነ​በ​ሩ​ትን የኮ​ረ​ብ​ታ​ውን መስ​ገ​ጃ​ዎች ካህ​ናት ሁሉ በመ​ሠ​ዊ​ያ​ዎቹ ላይ ገደ​ላ​ቸው፥ የሰ​ዎ​ቹ​ንም አጥ​ንት በመ​ሠ​ዊ​ያ​ዎቹ ላይ አቃ​ጠለ። ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ተመ​ለሰ።


የኤ​ል​ዛ​ቤ​ልም ሬሳ በኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤል እርሻ መሬት ላይ እንደ ፍግ ይሆ​ና​ልና ማንም፦ ይህች ኤል​ዛ​ቤል ናት ይል ዘንድ አይ​ች​ልም ብሎ የተ​ና​ገ​ረው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ይህ ነው” አለ።


ክፋ​ትን ወደ ጠላ​ቶች ይመ​ል​ሳ​ታል፤ በእ​ው​ነ​ት​ህም አጥ​ፋ​ቸው።


ትን​ቢት የሚ​ና​ገ​ሩ​ላ​ቸ​ውም ሰዎች ከራ​ብና ከሰ​ይፍ የተ​ነሣ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም መን​ገ​ዶች ይበ​ተ​ናሉ፤ ክፋ​ታ​ቸ​ው​ንም አፈ​ስ​ስ​ባ​ቸ​ዋ​ለ​ሁና እነ​ር​ሱ​ንና ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን፥ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም የሚ​ቀ​ብ​ራ​ቸው አይ​ገ​ኝም።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እጅ በላዬ ነበረ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በመ​ን​ፈሱ አወ​ጣኝ፤ አጥ​ን​ቶ​ችም በሞ​ሉ​በት ሸለቆ መካ​ከል አኖ​ረኝ።


መሠ​ዊ​ያ​ዎ​ቻ​ች​ሁም ይፈ​ር​ሳሉ፤ የፀ​ሐይ ምስ​ሎ​ቻ​ች​ሁም ይሰ​በ​ራሉ፤ የተ​ገ​ደሉ ሰዎ​ቻ​ች​ሁ​ንም በጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ችሁ ፊት እጥ​ላ​ለሁ።


የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ልጆች ሬሳ​ዎች በጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው ፊት አኖ​ራ​ለሁ፤ አጥ​ን​ቶ​ቻ​ች​ሁ​ንም በመ​ሠ​ዊ​ያ​ዎ​ቻ​ችሁ ዙሪያ እበ​ት​ና​ለሁ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “የኤ​ዶ​ም​ያ​ስን ንጉሥ አጥ​ንት አመድ እስ​ኪ​ሆን ድረስ አቃ​ጥ​ሎ​ታ​ልና ስለ ሦስት ወይም ስለ አራት የሞ​ዓብ ኀጢ​አት መቅ​ሠ​ፍ​ቴን ከማ​ድ​ረግ አል​መ​ለ​ስ​ላ​ቸ​ውም።