ኤርምያስ 13:2 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም ስለዚህ እግዚአብሔር እንዳዘዘኝ መቀነቱን ገዛሁ፤ ወገቤንም ታጠቅሁበት። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) እንደ ጌታም ቃል መታጠቂያን ገዛሁ ወገቤንም ታጠቅሁት። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ስለዚህ እግዚአብሔር ባዘዘኝ መሠረት መታጠቂያውን ገዝቼ ታጠቅሁት፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) እግዚአብሔርም እንዳለኝ የተልባ እግር መታጠቂያን ገዛሁ፤ ወገቤንም ታጠቅሁባት። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) እንደ እግዚአብሔርም ቃል መታጠቂያን ገዛሁ ወገቤንም ታጠቅሁባት። |
በዚያ ጊዜ እግዚአብሔር የአሞጽን ልጅ ኢሳይያስን፣ “ማቁን ከሰውነትህ፣ ጫማህን ከእግርህ አውልቅ” ሲል ተናገረው። እርሱም እንዲሁ አደረገ፤ ዕርቃኑንና ባዶ እግሩን ተመላለሰ።