መልካም ሥራውንና ያሳያቸውን ተኣምራቱን ረሱ፥
እርሱ የሠራውን ሥራ፣ ያሳያቸውንም ድንቅ ነገር ረሱ።
ያሳያቸውን ተአምራት ሁሉ እና ያደረገውን መልካም ነገር ሁሉ ረሱ።
የእስረኞች ጩኸት ወደ ፊትህ ይግባ፤ እንደ ክንድህም ታላቅነት የተገደሉትን ሰዎች ልጆች ጠብቃቸው።
ፈጥነውም ሥራውን ረሱ፥ ምክሩን እንኳን አልጠበቁም።
ተስፋቸውን በእግዚአብሔር እንዲያደርጉ፥ የእግዚአብሔርንም ሥራ እንዳይረሱ፥ ትእዛዙንም እንዲጠብቁ፥
በውኑ ኰረዳ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጣጌጥዋን ትረሳለችን? ሕዝቤ ግን በቍጥር ለማይቆጠሩ ቀናቶች ረስተውኛል።
የወለደህን አምላክ ተውህ፥ የፈጠረህን እግዚአብሔር ረሳህ።”