ኢዮብ 21:9 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ቤታቸው በሰላም ከፍርሃት ነጻ ነው፥ የእግዚአብሔርም በትር የለባቸውም። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ቤታቸው ያለ ሥጋት በሰላም ይኖራል፤ የእግዚአብሔርም በትር የለባቸውም። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ያለ አንዳች ሥጋት በሰላም ይኖራሉ፤ የእግዚአብሔር መቅሠፍት ደርሶባቸው አያውቅም፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ቤታቸው በብልፅግና የተሞላ ነው፤ የሚያስፈራቸውም የለም። ከእግዚአብሔርም ዘንድ መቅሠፍት አይመጣባቸውም። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ቤታቸው ከፍርሃት ወጥቶ የታመነ ነው፥ የእግዚአብሔርም በትር የለባቸውም። |