ምላስ መብልን እንደሚያጣጥም፥ ጆሮም ቃላትን ይለያልና።
ምላስ ምግብን አጣጥሞ እንደሚለይ፣ ጆሮም የንግግርን ለዛ ለይቶ ያውቃል።
የምግብ ጣዕም በምላስ እንደሚታወቅ፥ ንግግርም በጆሮ ይለያል።
ጆሮ ቃልን ትለያለችና፥ ጕሮሮም የመብልን ጣዕም ይለያል።
ትናጋ መብልን እንደሚቀምስ፥ ጆሮ ቃልን ትለያለችና።
ምላስ የምግብን ጣዕም እንደሚለይ፥ ጆሮም የቃላትን እውነት ይለይ የለምን?
ነገር ግን ነፍሱ እንዲጠፋ በመራገም አንደበቴ ኃጢአት እንዲሠራ አልፈቀድሁም፥
እነሆ፥ ለመናገር ተዘጋጅቻለሁ፥ አንደበቴም ቃላትን አሰናድቷል።
“እናንተ ጥበበኞች፥ ቃሌን ስሙ፥ እናንተም አዋቂዎች፥ ወደ እኔ አድምጡ።
ፍትሕን እንምረጥ፥ መልካሙንም ነገር በመካከላችን እንወቅ።
በውኑ በአንደበቴ በደል ይገኛልን? ምላሴ የተንኰልን ቃና መለየት አይችልምን?”
መንፈሳዊ ሰው ሁሉን ይመረምራል፤ እሱ ግን በማንም አይመረመርም።
ጠንካራ ምግብ የሚያስፈልጋቸው ግን መልካሙንና ክፉውን የመለየት ልምድ ያላቸው ብስለት ያላቸው ሰዎች ናቸው።