La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘካርያስ 13:3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ማንም ደግሞ ትንቢት ቢናገር የወለዱት አባቱና እናቱ፦ አንተ በእግዚአብሔር ስም ሐሰትን ተናግረሃልና በሕይወት አትኖርም ይሉታል፣ ትንቢትንም ሲናገር የወለዱት አባቱና እናቱ ይወጉታል።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ማንም ትንቢት ቢናገር ወላጅ አባትና እናቱ፣ ‘በእግዚአብሔር ስም ሐሰት ተናግረሃልና ሞት ይገባሃል’ ይሉታል። ትንቢት ሲናገርም የገዛ ወላጆቹ ይወጉታል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

አሁንም ቢሆን ማንም ትንቢት ቢናገር የወለዱት አባቱና እናቱ፦ “አንተ በጌታ ስም ሐሰትን ተናግረሃልና በሕይወት አትኖርም” ይሉታል። ትንቢትንም ሲናገር የወለዱት አባትና እናቱ ይወጉታል።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ማንም ነቢይ ነኝ ብሎ ቢነሣ የወለዱት አባቱና እናቱ በእግዚአብሔር ስም ሐሰትን ስለ ተናገርክ መሞት አለብህ ይሉታል፤ ትንቢትም ሲናገር ወላጆቹ ወግተው ይገድሉታል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ማንም ደግሞ ትንቢት ቢናገር የወለዱት አባቱና እናቱ፦ አንተ በእግዚአብሔር ስም ሐሰትን ተናግረሃልና በሕይወት አትኖርም ይሉታል፥ ትንቢትንም ሲናገር የወለዱት አባቱና እናቱ ይወጉታል።

Ver Capítulo



ዘካርያስ 13:3
13 Referencias Cruzadas  

ሕል​ምን አለ​ምን እያሉ በስሜ ሐሰ​ተኛ ትን​ቢት የሚ​ና​ገ​ሩ​ትን የነ​ቢ​ያ​ትን ነገር ሰም​ቻ​ለሁ።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሸክም የሚ​ለ​ውን ነቢ​ይ​ንና ካህ​ንን፥ ሕዝ​ብ​ንም ያን ሰውና ቤቱን እቀ​ጣ​ለሁ።


ነቢ​ዩም ኤር​ም​ያስ ሐሰ​ተ​ኛ​ውን ሐና​ን​ያን፥ “ሐና​ንያ ሆይ ስማ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አል​ላ​ከ​ህም፤ ነገር ግን ይህ ሕዝብ በሐ​ሰት እን​ዲ​ታ​መን አድ​ር​ገ​ሃል።


ስለ​ዚህ፥ ሐሰ​ትን አታ​ዩም፤ እን​ግ​ዲ​ህም ከንቱ ምዋ​ር​ትን አታ​ም​ዋ​ር​ቱም፤ ሕዝ​ቤ​ንም ከእ​ጃ​ችሁ አድ​ና​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።”


ነቢ​ዩም ቢታ​ለል፥ ቃል​ንም ቢና​ገር፥ ያን ነቢይ ያታ​ለ​ልሁ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነኝ፥ እጄ​ንም በእ​ርሱ ላይ እዘ​ረ​ጋ​ለሁ፤ ከሕ​ዝ​ቤም ከእ​ስ​ራ​ኤል መካ​ከል አጠ​ፋ​ዋ​ለሁ።


እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “የሰው ልጅ ሆይ! በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች መካ​ከል ለዘ​ለ​ዓ​ለም የም​ቀ​መ​ጥ​በት የዙ​ፋኔ ስፍ​ራና የእ​ግሬ ጫማ መረ​ገጫ ይህ ነው። ዳግ​መ​ኛም የእ​ስ​ራ​ኤል ቤትና ነገ​ሥ​ታ​ቶ​ቻ​ቸው በዝ​ሙ​ታ​ቸ​ውና በከ​ፍ​ታ​ዎ​ቻ​ቸው በአ​ለው በነ​ገ​ሥ​ታ​ቶ​ቻ​ቸው ሬሳ ቅዱስ ስሜን አያ​ረ​ክ​ሱም።


ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።


“ወደ እኔ የሚ​መጣ፥ ሊከ​ተ​ለ​ኝም የሚ​ወድ አባ​ቱ​ንና እና​ቱን፥ ሚስ​ቱ​ንና ልጆ​ቹን፥ ወን​ድ​ሞ​ቹ​ንና እኅ​ቶ​ቹን፥ የራ​ሱ​ንም ሰው​ነት እንኳ ቢሆን የማ​ይ​ጠላ ደቀ መዝ​ሙሬ ሊሆን አይ​ች​ልም።


ስለ​ዚህ ከአ​ሁን ጀምሮ በሥጋ የም​ና​ው​ቀው የለም፤ ክር​ስ​ቶ​ስ​ንም በሥጋ ብና​ው​ቀው አሁን ግን ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ የም​ና​ው​ቀው አይ​ደ​ለም።


ነገር ግን ይና​ገር ዘንድ ያላ​ዘ​ዝ​ሁ​ትን ቃል በስሜ የሚ​ና​ገር ነቢይ፥ በሌላ አማ​ል​ክት ስም የሚ​ና​ገር ነቢ​ይም፥ እርሱ ይገ​ደል።


እና​ቱ​ንና አባ​ቱን አላ​የ​ኋ​ች​ሁም ላለ፥ ወን​ድ​ሞ​ቹ​ንም ላላ​ወቀ፥ ልጆ​ቹ​ንም ላላ​ስ​ተ​ዋለ፤ ቃል​ህን ለጠ​በቀ፥ በቃል ኪዳ​ን​ህም ለተ​ማ​ጠነ።