ለመክበራቸው እጆቻቸውን ይቀድሱ ዘንድ በተቀደሱበት በዚያ ቦታ ይብሉት፤ የባዕድ ልጅ ግን አይብላው፤ የተቀደሰ ነውና።
ዘሌዋውያን 10:18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) እነሆ፥ ደሙን ወደ መቅደስ ውስጥ አላገባችሁትም፤ እኔ እንደታዘዝሁ በቅዱስ ስፍራ ውስጥ ትበሉት ዘንድ ይገባችሁ ነበር።” አዲሱ መደበኛ ትርጒም ደሙ ወደ ተቀደሰው ስፍራ ስላልገባ፣ በሰጠሁት ትእዛዝ መሠረት ፍየሉን በተቀደሰው ስፍራ መብላት ይገባችሁ ነበር።” መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) እነሆ፥ ደሙን ወደ መቅደሱ ውስጥ አላገባችሁትም፤ እኔ እንደ ታዘዝሁ በቅዱሱ ስፍራ ውስጥ ትበሉት ይገባችሁ ነበር።” አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ደሙ ወደተቀደሰው ድንኳን ስላልገባ እኔ ባዘዝኳችሁ መሠረት በዚያው በተቀደሰው ስፍራ የቀረበውን መሥዋዕት መመገብ ነበረባችሁ።” መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) እነሆ ደሙን ወደ መቅደሱ ውስጥ አላገባችሁትም፤ እኔ እንዳዘዝሁ በቅዱሱ ስፍራ ውስጥ ትበሉት ዘንድ ይገባችሁ ነበር አላቸው። |
ለመክበራቸው እጆቻቸውን ይቀድሱ ዘንድ በተቀደሱበት በዚያ ቦታ ይብሉት፤ የባዕድ ልጅ ግን አይብላው፤ የተቀደሰ ነውና።
ነገር ግን በመቅደሱ ውስጥ ለማስተስረያ ይሆን ዘንድ ከደሙ ወደ ምስክሩ ድንኳን የሚገባው የኀጢአት መሥዋዕት ሁሉ አይበላም፤ በእሳት ይቃጠላል።