La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኢያሱ 9:17 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ተጕ​ዘው በሦ​ስ​ተ​ኛው ቀን ወደ ከተ​ሞ​ቻ​ቸው ደረሱ፤ ከተ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ገባ​ዖን፥ ከፊራ፥ ብኤ​ሮ​ትና ኢያ​ሪም ነበሩ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ስለዚህ እስራኤላውያን ተጕዘው በሦስተኛው ቀን ገባዖን፣ ከፊራ፣ ብኤሮትና ቂርያትይዓይሪም ወደተባሉት የገባዖን ሰዎች ወደሚኖሩባቸው ከተሞች መጡ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

የእስራኤልም ልጆች ተጉዘው በሦስተኛው ቀን ወደ ከተሞቻቸው መጡ፤ ከተሞቻቸው ገባዖን፥ ከፊራ፥ ብኤሮት፥ ቂርያት-ይዓሪም ነበሩ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ስለዚህም የእስራኤል ሕዝብ ጒዞ ጀምረው ከሦስት ቀን በኋላ እነዚህ ሕዝብ ወደሚኖሩባቸው ከተሞች ደረሱ፤ ከተሞቻቸውም ገባዖን፥ ከፊራ፥ በኤሮትና ቂርያትይዓሪም ተብለው ይጠሩ ነበር፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

የእስራኤልም ልጆች ተጉዘው በሦስተኛው ቀን ወደ ከተሞቻቸው መጡ፥ የከተሞቻቸውም ስም ገባዖን፥ ከፊራ፥ ብኤሮት፥ ቂርያትይዓሪም ነበረ።

Ver Capítulo



ኢያሱ 9:17
24 Referencias Cruzadas  

ለሳ​ኦ​ልም ልጅ ለኢ​ያ​ቡ​ስቴ የጭ​ፍራ አለ​ቆች የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበ​ሩት፤ የአ​ን​ደ​ኛው ስም በዓና፥ የሁ​ለ​ተ​ኛ​ውም ስም ሬካብ ነበረ፤ ከብ​ን​ያ​ምም ልጆች የቤ​ሮ​ታ​ዊው የሬ​ሞን ልጆች ነበሩ፤ ቤሮ​ትም ለብ​ን​ያም ተቈ​ጥራ ነበር።


ገባ​ዖ​ና​ዊው ሰማ​ያስ፥ እርሱ በሠ​ላ​ሳው መካ​ከ​ልና በሠ​ላ​ሳው ላይ ኀያል ሰው ነበረ፤ ኤር​ም​ያስ፥ ሕዝ​ኤል፥ ዮሐ​ናን፥ ገድ​ሮ​ታዊ ዮዛ​ባት፤


የካ​ሌ​ብም ልጆች እነ​ዚህ ነበሩ፤ የኤ​ፍ​ራታ የበ​ኵሩ የኦር ልጅ የቀ​ር​ያ​ታ​ርም አባት ሶባል ነበር፥


የቀ​ር​ያ​ታ​ር​ምም አባት የሶ​ባል ልጆች አረኤ፥ ሃጼ፥ አማ​ኒት ነበሩ።


የቀ​ር​ያ​ታ​ርም ወገ​ኖች፤ ይት​ራ​ው​ያን፥ ፋታ​ው​ያን፥ ሹማ​ታ​ው​ያን፥ ሚሸ​ራ​ው​ያን፤ ከእ​ነ​ዚ​ህም ሶራ​ሐ​ው​ያ​ንና ኤሽ​ታ​አ​ላ​ው​ያን ወጡ።


ሙሴም በም​ድረ በዳ የሠ​ራት የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማደ​ሪ​ያና ለሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ሆ​ነው መሠ​ዊያ በዚ​ያን ጊዜ በገ​ባ​ዖን ባለው በኮ​ረ​ብ​ታው መስ​ገጃ ነበሩ።


የቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪ​ምና የቃ​ፌር፥ የብ​ኤ​ሮ​ትም ልጆች ሰባት መቶ አርባ ሦስት።


የቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪ​ምና የቃ​ፌር፥ የቤ​ሮ​ትም ሰዎች ሰባት መቶ አርባ ሦስት።


ደግ​ሞም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም ትን​ቢት የተ​ና​ገረ አንድ ሰው ነበር፤ እር​ሱም የቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪም ሰው የሸ​ማያ ልጅ ኡርያ ይባል ነበር፤ በዚ​ችም ከተማ፥ በዚ​ችም ምድር ላይ እንደ ኤር​ም​ያስ ቃል ሁሉ ትን​ቢት ተና​ገረ።


ገባ​ዖን ከመ​ን​ግ​ሥ​ታት ከተ​ሞች እንደ አን​ዲቱ ታላቅ ከተማ ስለ​ሆ​ነች፥ ከጋ​ይም ስለ በለ​ጠች፥ ሰዎ​ች​ዋም ሁሉ ኀያ​ላን ስለ ነበሩ እጅግ ፈራ።


ቴቆ፥ ኤፍ​ራታ፥ ይኽ​ች​ውም ቤተ ልሔም ናት፤ ፋጎ​ርም፥ ኤጣ​ንም፥ ቁሎን፥ ጠጦ​ንም፥ ሶብ​ሄም፥ ቃሬም፥ ጌሌም፥ ኤቴር፥ መነ​ኮም፥ ዐሥራ አንድ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው፥ ቅር​ያ​ት​በ​ኣል፥ ይኽ​ች​ውም የኢ​ያ​ርም ከተማ ናት፤ ሶቤታ፥ ሁለቱ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።


ድን​በ​ሩም ከተ​ራ​ራው ራስ ወደ ኔፍቶ ውኃ ምንጭ ይሄ​ዳል፤ ወደ ዔፍ​ሮ​ንም ተራራ ይደ​ር​ሳል፤ ወደ ኢያ​ሪም ከተማ ወደ በኣላ ይደ​ር​ሳል።


ድን​በ​ሩም ወደ ባሕር ሄደ፤ በቤ​ቶ​ሮ​ንም ፊት ለፊት ካለው ተራራ ወደ አዜብ ዞረ፤ መው​ጫ​ውም ቂር​ያ​ታ​ርም በም​ት​ባል በይ​ሁዳ ልጆች ከተማ በቂ​ር​ያ​ት​በ​ኣል ነበረ፤ ይህ በባ​ሕር በኩል ነበረ።


የደ​ቡ​ብም ዳርቻ ከቅ​ር​ያ​ታ​ርም መጨ​ረሻ ነበረ፤ ድን​በ​ሩም በጋ​ሲን ላይ ወደ ነፍቶ ውኃ ምንጭ ወጣ።


ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር ቃል ኪዳን ካደ​ረጉ ከሦ​ስት ቀን በኋላ ከቅ​ርብ እን​ደ​ሆ​ኑና በአ​ጠ​ገ​ባ​ቸው እን​ደ​ሚ​ኖሩ ሰሙ።


የማ​ኅ​በ​ሩም አለ​ቆች በእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ ማሉ​ላ​ቸው የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች አል​ገ​ደ​ሉ​አ​ቸ​ውም። ማኅ​በ​ሩም ሁሉ በአ​ለ​ቆቹ ላይ አጕ​ረ​መ​ረሙ።


በገ​ባ​ዖን የሚ​ኖሩ ሰዎች ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በኢ​ያ​ሪ​ኮና በጋይ ያደ​ረ​ገ​ውን በሰሙ ጊዜ፥


እነ​ር​ሱም አሉት፥ “በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም እጅግ ከራቀ ሀገር ባሪ​ያ​ዎ​ችህ መጥ​ተ​ናል፤ ዝና​ው​ንም፥ በግ​ብ​ፃ​ው​ያ​ንም ያደ​ረ​ገ​ውን ሁሉ፥


ወጥ​ተ​ውም በይ​ሁዳ ቂር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪም ሰፈሩ፤ ስለ​ዚ​ህም የዚያ ስፍራ ስም እስከ ዛሬ ድረስ የዳን ሰፈር ተብሎ ተጠራ፤ እነ​ሆም፥ ቦታዉ ከቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪም በስ​ተ​ኋላ ነው።


በቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪ​ምም ወደ ተቀ​መ​ጡት ሰዎች መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ልከው፥ “ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት መል​ሰ​ዋል፤ ወር​ዳ​ች​ሁም ወደ እና​ንተ ውሰ​ዱ​አት” አሉ።


የቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪም ሰዎ​ችም መጥ​ተው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የቃል ኪዳን ታቦት አወጡ፤ በኮ​ረ​ብ​ታ​ውም ላይ ወዳ​ለው ወደ አሚ​ና​ዳብ ቤት አገ​ቡ​አት፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ታቦት እን​ዲ​ጠ​ብቅ ልጁን አል​ዓ​ዛ​ርን ቀደ​ሱት።