La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኢያሱ 19:10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ሦስ​ተ​ኛ​ውም ዕጣ ለዛ​ብ​ሎን ልጆች በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው ወጣ፤ የር​ስ​ታ​ቸ​ውም ድን​በር እስከ ኤሴ​ዴቅ ጎላ ነበረ፤

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሦስተኛው ዕጣ ለዛብሎን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ የርስታቸውም ድንበር እስከ ሣሪድ ይደርሳል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ሦስተኛውም ዕጣ ለዛብሎን ልጆች በየወገኖቻቸው ወጣ፤ የርስታቸውም ድንበር እስከ ሣሪድ ደረስ ይደርስ ነበር፤

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ሦስተኛው ዕጣ ለዛብሎን ነገድ በየወገናቸው ወጣ፤ እነርሱም የተቀበሉት ርስት እስከ ሣሪድ ይደርሳል፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ሦስተኛውም ዕጣ ለዛብሎን ልጆች በየወገኖቻቸው ወጣ፥ የርስታቸውም ድንበር ወደ ሣሪድ ደረሰ፥

Ver Capítulo



ኢያሱ 19:10
8 Referencias Cruzadas  

የልያ ልጆች፤ የያ​ዕ​ቆብ በኵር ልጅ ሮቤል፥ ስም​ዖን፥ ሌዊ፥ ይሁዳ፥ ይሳ​ኮር፥ ዛብ​ሎን፤


“ዛብ​ሎን ጫማ​ውን አዝቦ ይኖ​ራል፤ እር​ሱም እንደ መር​ከ​ቦች ወደብ ይሆ​ናል፤ ዳር​ቻ​ውም እስከ ሲዶና ይሰ​ፋል።


ከይ​ሳ​ኮ​ርም ድን​በር ቀጥሎ ከም​ሥ​ራቅ ጀምሮ እስከ ምዕ​ራብ ድረስ ለዛ​ብ​ሎን አንድ የዕጣ ክፍል ይሆ​ናል።


የብ​ን​ያ​ምም ነገድ ዕጣ በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው በቅ​ድ​ሚያ ወጣ፤ የዕ​ጣ​ቸ​ውም ዳርቻ በይ​ሁዳ ልጆ​ችና በዮ​ሴፍ ልጆች መካ​ከል ወጣ።


እና​ን​ተም ምድ​ሪ​ቱን በሰ​ባት ክፍል ክፈ​ሏት፤ ወደ እኔም ወዲህ አም​ጡ​ልኝ፤ በአ​ም​ላ​ካ​ች​ንም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት በዚህ ዕጣ አጣ​ጥ​ላ​ች​ኋ​ለሁ።


ድን​በ​ራ​ቸ​ውም በም​ዕ​ራብ በኩል ወደ ማራ​ጌላ ይወ​ጣል፤ እስከ ቤተ ራባም ይደ​ር​ሳል፤ በኢ​ያ​ቃ​ንም ፊት ለፊት ወዳ​ለው ሸለ​ቆም ይደ​ር​ሳል፤


ከይ​ሁዳ ልጆች ክፍል የስ​ም​ዖን ልጆች ርስት ሆነ፤ የይ​ሁ​ዳም ልጆች ዕድል ፋንታ ስለ በዛ​ባ​ቸው የስ​ም​ዖን ልጆች በር​ስ​ታ​ቸው መካ​ከል ወረሱ።