Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ዘፍጥረት 35:23 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

23 የልያ ልጆች፤ የያ​ዕ​ቆብ በኵር ልጅ ሮቤል፥ ስም​ዖን፥ ሌዊ፥ ይሁዳ፥ ይሳ​ኮር፥ ዛብ​ሎን፤

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

23 የልያ ልጆች፦ የያዕቆብ የበኵር ልጅ ሮቤል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፤

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

23 የልያ ልጆች፥ የያዕቆብ በኩር ልጅ ሮቤል፥ ስምዖን፥ ሌዊ፥ ይሁዳ፥ ይሳኮር፥ ዛብሎን፥

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

23 የልያ ልጆች፥ የያዕቆብ የመጀመሪያ ልጅ ሮቤል፥ ስምዖን፥ ሌዊ፥ ይሁዳ፥ ይሳኮርና ዛብሎን ናቸው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

23 የያዕቆብም ልጆች አሥራ ሁለት ናቸው የልያ ልጆች የያዕቆብ በኵር ልጅ ሮቤል ስምዖን፥ ሌዊ፥ ይሁዳ፥ ይሳኮር፥ ዛብሎን፤

Ver Capítulo Copiar




ዘፍጥረት 35:23
33 Referencias Cruzadas  

ለላ​ባም ሁለት ሴቶች ልጆች ነበ​ሩት፤ የታ​ላ​ቂቱ ስም ልያ የታ​ና​ሺ​ቱም ስም ራሔል ነበረ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ልያ የተ​ጠ​ላች መሆ​ን​ዋን በአየ ጊዜ ማኅ​ፀ​ን​ዋን ከፈ​ተ​ላት፤ ራሔል ግን መካን ነበ​ረች።


ዕቁ​ባ​ቶ​ቹ​ንና ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም በፊት አደ​ረገ፤ ልያ​ንና ልጆ​ች​ዋን በኋላ፥ ራሔ​ል​ንና ዮሴ​ፍ​ንም ከሁሉ በኋላ አደ​ረገ።


“ሮቤል እርሱ የበ​ኵር ልጄና ኀይሌ፥ የል​ጆ​ችም መጀ​መ​ሪያ ነው፤ ክፉ ሆነ፤ አን​ገ​ቱ​ንም አደ​ነ​ደነ። ጭንቅ ነገ​ር​ንም አደ​ረገ።


ለሰ​ልፍ ጽኑ​ዓን ኀያ​ላን ሰዎች የነ​በሩ የስ​ም​ዖን ልጆች ሰባት ሺህ አንድ መቶ ነበሩ።


በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ነገ​ዶች ላይ እነ​ዚህ ነበሩ፦ በሮ​ቤ​ላ​ው​ያን ላይ የዝ​ክሪ ልጅ ኤል​ያ​ዛር አለቃ ነበረ፤ በስ​ም​ዖ​ና​ው​ያን ልጅ የመ​ዓካ ልጅ ሰፋ​ጥ​ያስ ነበረ፤


ከአ​ባ​ታ​ቸው ከያ​ዕ​ቆብ ጋር ወደ ግብፅ የገ​ቡት የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ስሞች እነ​ዚህ ናቸው፤ ሰው ሁሉ ከቤተ ሰቡ ጋር ገባ፤


“የከ​ተ​ማ​ዪ​ቱም መው​ጫ​ዎች እነ​ዚህ ናቸው። በሰ​ሜን ወገን ልኩ አራት ሺህ አም​ስት መቶ ክንድ ነው።


የእ​ስ​ራ​ኤል በኵር የሮ​ቤል ልጆች በየ​ት​ው​ል​ዳ​ቸው፥ በየ​ወ​ገ​ና​ቸው፥ በየ​አ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ቤቶች እንደ እየ​ስ​ማ​ቸው ቍጥር፥ በየ​ራ​ሳ​ቸው፥ ከሃያ ዓመት ጀምሮ ከዚ​ያም በላይ ያለው ወንድ ሁሉ፥ ወደ ሰልፍ የሚ​ወ​ጡት ሁሉ፥


ከእ​ና​ን​ተም ጋር የሚ​ቆ​ሙት ሰዎች ስሞ​ቻ​ቸው እነ​ዚህ ናቸው፤ ከሮ​ቤል የሰ​ዲ​ዮር ልጅ ኤሊ​ሱር፥


በመ​ጀ​መ​ሪ​ያም የይ​ሁዳ ልጆች ሰፈር በሥ​ር​ዐ​ታ​ቸው ከየ​ሠ​ራ​ዊ​ቶ​ቻ​ቸው ጋር ተጓዘ፤ በሠ​ራ​ዊ​ቱም ላይ የአ​ሚ​ና​ዳብ ልጅ ነአ​ሶን አለቃ ነበረ።


ስማ​ቸ​ውም ይህ ነበረ፤ ከሮ​ቤል ነገድ የዝ​ኩር ልጅ ሰሙ​ኤል፤


በመ​ጀ​መ​ሪያ በም​ሥ​ራቅ በኩል የሚ​ሰ​ፍ​ሩት ከሠ​ራ​ዊ​ቶ​ቻ​ቸው ጋር የይ​ሁዳ ሰፈር ሰዎች ይሆ​ናሉ፤ የይ​ሁዳ ልጆ​ችም አለቃ የአ​ሚ​ና​ዳብ ልጅ ነአ​ሶን ነበረ።


የእ​ስ​ራ​ኤል በኵር ሮቤል፤ የሮ​ቤል ልጆች፤ ከሄ​ኖኅ የሄ​ኖ​ኃ​ው​ያን ወገን፤ ከፈ​ሉስ የፈ​ሉ​ሳ​ው​ያን ወገን።


የሰ​ዎ​ቹም ስም ይህ ነው፤ ከይ​ሁዳ ነገድ የዮ​ፎኒ ልጅ ካሌብ፥


በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ውም ቀን መባ​ውን ያቀ​ረበ ከይ​ሁዳ ነገድ የአ​ሚ​ና​ዳብ ልጅ ነአ​ሶን ነበረ።


የግ​ዝ​ረ​ት​ንም ኪዳን ሰጠው፤ ከዚ​ህም በኋላ ይስ​ሐ​ቅን ወለደ፤ በስ​ም​ን​ተ​ኛው ቀንም ገረ​ዘው፤ እን​ዲሁ ይስ​ሐ​ቅም ያዕ​ቆ​ብን፥ ያዕ​ቆ​ብም ዐሥራ ሁለ​ቱን የቀ​ደሙ አባ​ቶ​ችን ገረዙ።


ሙሴም በዚያ ቀን እን​ዲህ ብሎ ሕዝ​ቡን አዘዘ፦


ሮቤ​ልን እፈ​ል​ገ​ዋ​ለሁ፤ አይ​ሙ​ት​ብኝ፤ ቍጥ​ሩም ብዙ ይሁን።


ሙሴም ለሮ​ቤል ነገድ በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ርስ​ትን ሰጣ​ቸው።


የይ​ሁ​ዳም ነገድ ድን​በር በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ከኤ​ዶ​ም​ያስ ዳርቻ፥ ከጺን ምድረ በዳ ጀምሮ በዐ​ዜብ በኩል እስከ ቃዴስ ድረስ ነው።


ሁለ​ተ​ኛ​ውም ዕጣ ለስ​ም​ዖን ልጆች ነገድ በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው ወጣ፤ ርስ​ታ​ቸ​ውም በይ​ሁዳ ልጆች ርስት መካ​ከል ነበረ።


ሦስ​ተ​ኛ​ውም ዕጣ ለዛ​ብ​ሎን ልጆች በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው ወጣ፤ የር​ስ​ታ​ቸ​ውም ድን​በር እስከ ኤሴ​ዴቅ ጎላ ነበረ፤


አራ​ተ​ኛ​ውም ዕጣ ለይ​ሳ​ኮር ልጆች ወጣ።


ከስምዖን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፥ ከሌዊ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፥ ከይሳኮር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፥


በአ​ማ​ሌቅ ዘንድ ሥር የነ​በ​ራ​ቸው እነ​ርሱ ከኤ​ፍ​ሬም፥ ብን​ያም ሆይ! በሕ​ዝብ መካ​ከል ከአ​ንተ በኋላ ወረዱ፤ አለ​ቆች ከማ​ኪር፥ የን​ጉ​ሥ​ንም ዘንግ የሚ​ይዙ ከዛ​ብ​ሎን ወረዱ።


የይ​ሳ​ኮ​ርም አለ​ቆች ከዲ​ቦራ ጋር ነበሩ፤ ይሳ​ኮ​ርም እንደ ባርቅ ነበረ፤ ከእ​ግሩ በኋላ ወደ ሸለ​ቆው ቸኮሉ፤ በሮ​ቤል ፈሳ​ሾች አጠ​ገብ ብዙ የልብ ማመ​ን​ታት ነበረ።


ዛብ​ሎን ነፍ​ሱን ወደ ሞት ያሳ​ለፈ ሕዝብ ነው፤ ንፍ​ታ​ሌ​ምም በሀ​ገሩ ኮረ​ብታ ላይ ነው።


በከተማይቱ በር አደባባይም የነበሩ ሕዝብ ሁሉ ሽማግሌዎቹም፦ እኛ ምስክሮች ነን፣ እግዚአብሔር ይህችን ወደ ቤትህ የምትገባውን ሴት የእስራኤልን ቤት እንደ ሠሩ እንደ ሁለቱ እንደ ራሔልና እንደ ልያ ያድርጋት፣ አንተም በኤፍራታ ባለ ጠጋ ሁን፥ ስምህም በቤተ ልሔም ይጠራ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos