La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዕዝራ 7:26 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የአ​ም​ላ​ክ​ህ​ንም ሕግ፥ የን​ጉ​ሡ​ንም ሕግ በማ​ያ​ደ​ርግ ሁሉ ላይ ሞት፥ ወይም ስደት፥ ወይም ገን​ዘብ መወ​ረስ፥ ወይም ግዞት በፍ​ጥ​ነት ይፈ​ረ​ድ​በት።”

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ለአምላክህ ሕግና ለንጉሡ ሕግ የማይታዘዝ ማንኛውም ሰው፣ የሞት ወይም የስደት ወይም የንብረት መወረስ ወይም የእስራት ቅጣት ይፈጸምበት።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

የአምላክህን ሕግና የንጉሡን ትእዛዝ በማያደርግ በማንም ላይ ሞት ወይም ስደት ወይም ንብረት መወረስ ወይም ግዞት በፅኑ ይፈረድበት።”

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ለእግዚአብሔር ሕግ ወይም ለመንግሥት ሕግ ሁሉ የማይታዘዝ ማንም ሰው ቢኖር በጥንቃቄ እየተመረመረ በሞት ወይም ከሀገር በመባረር ወይም ሀብት ንብረቱን በመወረስ ወይም በእስራት ይቀጣ።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

የአምላክህንም ሕግ፥ የንጉሡንም ሕግ በማያደርግ ሁሉ ላይ ሞት ወይም ስደት ወይም ገንዘብን መወረስ ወይም ግዞት በፍጥነት ይፈረድበት።”

Ver Capítulo



ዕዝራ 7:26
12 Referencias Cruzadas  

ደግ​ሞም አንድ ልብ ይሰ​ጣ​ቸው ዘንድ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል የሆ​ነ​ውን የን​ጉ​ሡ​ንና የአ​ለ​ቆ​ቹን ትእ​ዛዝ ያደ​ርጉ ዘንድ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ በእ​ነ​ርሱ ላይ ሆነ።


ይህም ነገር ለአ​ንተ ይገ​ባ​ልና፥ እኛም ከአ​ንተ ጋር ነንና ተነሣ፤ በርታ፤ አድ​ር​ገ​ውም።”


“እስከ ሦስት ቀን ድረስ የማ​ይ​መጣ ሁሉ እንደ ሽማ​ግ​ሎ​ችና እን​ዳ​ለ​ቆች ምክር ከብቱ ሁሉ ይበ​ዝ​በዝ፤ እር​ሱም ከም​ር​ኮው ጉባኤ ይለይ” ብሎ ዐዋጅ አስ​ነ​ገረ።


ይህ​ንም ትእ​ዛዝ የሚ​ለ​ውጥ ሁሉ ምሰ​ሶው ከቤቱ ተነ​ቅሎ እርሱ ይሰ​ቀ​ል​በት፤ በላ​ዩም ይገ​ደል፤ ቤቱም የጕ​ድፍ መጣያ ይደ​ረግ ብዬ አዝ​ዣ​ለሁ።


ስሙ በዚያ የሚ​ኖር አም​ላክ ይህን ይለ​ውጡ ዘንድ፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ​ው​ንም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ያፈ​ር​ሱት ዘንድ እጃ​ቸ​ውን የሚ​ዘ​ረ​ጉ​ትን ነገ​ሥ​ታ​ትና አሕ​ዛብ ሁሉ ያጥፋ። እኔ ዳር​ዮስ ይህን አዝ​ዣ​ለሁ፤ በት​ጋት ይፈ​ጸም።”


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የግ​ብ​ዞ​ችን አጥ​ን​ቶች በት​ኖ​አ​ልና በዚያ የሚ​ያ​ስ​ፈራ ሳይ​ኖር እጅግ ፈሩ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አዋ​ር​ዶ​አ​ቸ​ዋ​ልና አፈሩ።


“የዚ​ህን ሕግ ቃሎች ያደ​ርግ ዘንድ የማ​ያ​ጸና ርጉም ይሁን፤ ሕዝ​ቡም ሁሉ አሜን ይላሉ።