በሬው ግን ከትናንትና ከትናንት ወዲያ ተዋጊ ቢሆን፥ ሰዎችም ለባለቤቱ ቢመሰክሩለት ባያስወግደውም፥ ወንድን ወይም ሴትን ቢገድል፥ በሬው ይወገር፤ ባለቤቱ ደግሞ ይገደል።
ዘፀአት 21:36 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በሬውም ትናንትና ከትናንት ወዲያ ተዋጊ መሆኑ ቢታወቅ ለባለቤቱም ቢመሰክሩለት፥ ባለቤቱም ባያስወግደው በሬውን በበሬው ፋንታ ይስጥ፤ የሞተውም ለእርሱ ይሁነው። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ሆኖም በሬው የመዋጋት ዐመል ያለው መሆኑ ከታወቀ፣ ባለቤቱም በረት ሳይዘጋበት ቢቀር፣ ባለቤቱ በሬውን በበሬው ፈንታ ይክፈል፤ የሞተውም እንስሳ ለርሱ ይሆናል። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በሬው አስቀድሞ ተዋጊ መሆኑ ቢታወቅ፥ ባለቤቱም ባይጠብቀው፥ በሬውን በበሬው ፈንታ ይስጥ፥ የሞተውም ለእርሱ ይሁነው። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ነገር ግን በሬው ተዋጊ መሆኑ ታውቆ ሳለ ባለቤቱ በበረት ውስጥ ሳይዘው ቀርቶ ከሆነ፥ በሬው ለሞተበት ሰው አንድ በሕይወት ያለ በሬ ካሣ ይክፈል፤ የሞተውንም በሬ ለራሱ ያስቀር።” መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በሬውም አስቀድሞ ተዋጊ መሆኑ ቢታወቅ፥ ባለቤቱም ባይጠብቀው፥ በሬውን በበሬው ፈንታ ይስጥ፥ የሞተውም ለእርሱ ይሁነው። |
በሬው ግን ከትናንትና ከትናንት ወዲያ ተዋጊ ቢሆን፥ ሰዎችም ለባለቤቱ ቢመሰክሩለት ባያስወግደውም፥ ወንድን ወይም ሴትን ቢገድል፥ በሬው ይወገር፤ ባለቤቱ ደግሞ ይገደል።
“የሰው በሬ የሌላውን በሬ ቢወጋ፥ ቢሞትም፥ ደኅናውን በሬ ይሽጡ፤ ዋጋውንም በትክክል ይካፈሉ፤ የሞተውንም ደግሞ በትክክል ይካፈሉ።
“ሰው በሬ ወይም በግ ቢሰርቅ፥ ቢያርደው ወይም ቢሸጠው፥ በአንድ በሬ ፋንታ አምስት በሬዎች፥ በአንድ በግም ፋንታ አራት በጎች ይክፈል።